በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ

Logo of telegram channel bewketuseyoum19 — በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ
Topics from channel:
Meri
Block
Ethiopia
Fiker
Size
Баллон
Join
Share
Shaer
Available
All tags
Channel address: @bewketuseyoum19
Categories: Courses & guides
Language: English
Subscribers: 94.12K
Description from channel

➲የበእውቀቱ ስዩም ፈገግታም እውቀትም የሚሰጡ ወጎች ፣ ግጥምች እና የተለያዩ ፀሀፊዎች የስነጽሑፍ ስራዎች የሚቀርብበት ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
@bewketuseyoum19
✥--------------------✥
For your comment,feedback and promotion @Bewketuseyoum2bot
Thank you!

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 3

2023-03-21 14:43:50 እናልቅስ እየሳቅን ማንም ሳያይብን

ከጣራችን በታች በአንድ አይን ተኝተን ፣
መንቃት ብርቅ ሁኖብን
ከሞት ጋር እያደርን ፣
በተለጎመ አፍ በተቀየደ አንገት ፣
ድምፃችን ተሰልቦ (እ'ም)ንናገርበት ፣
ታፍኖ እየቀረ መራራችን እውነት ፣
ሰዎች ተቀንሰው ትውልድ በሌሉበት ፣
ደም እያቀለሙ
ብራናው ቢከተብ ቆዳው እየለፋ ፣
መጽሐፍ ምን ያደርጋል ታሪክ እየጠፋ ፣

ተስፋ እያደረግን ህልም ቢታለምም ፣
ሰቆቃና ለቅሶ በበዛበት ዓለም ፣
ከልብ እንደመሳቅ ስኬት እኮ የለም!

         ተፃፈ ፦ በብስሩ አዳም

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.1K viewsAbela, 11:43
Open / Comment
2023-03-21 08:50:19 አስጨርሱኝ
(በእውቀቱ ስዩም)

አብቹ ወደ ስልጣን በመጣ ሰሞን ለቀቅ ያረግሁትን ሙገሳ ብጤ፥ ከማህደሬ ፈልፍላችሁ በማውጣት “ ሙድ “ ለመያዝ የምትሞክሩ ሰዎች፥ ዲያብሎስ በብርድ ቀን፥ ቆለጣችሁን በጋመ ወረንጦ ይያዝላችሁ ከማለት ውጭ ክፉ አይወጣኝም!

በጊዜው ከነበረው የማሽቃበጥ ፏፏቴ አንጻር ሲታይኮ የኔ ግሳጼ ነው ማለት ይቻላል: በጊዜው ማሽቃበጡን ከፊት ሆነው ሲመሩት ከነበሩት አርቲስቶች አንዱ በቅርቡ “ ይሄ ስሙን ልጠራው የማልፈልገው ሰውየ” ሲል ሰማሁት፤ ለሽንገላ የፈጠነ ለርግማንም የሚቀድመው የለም፤ እኛ ግን ዛሬም በሚሆነው አዝነን፥ ሂስ ስናቀርብ “ ክቡር ጠቅላይ ምኒስትር “ የሚል ማእረጋቸውን አንነሳቸውም ::

ብቻ የሆነውን ሁሉ ሳስበው የልጅነቴን አንድ ገጠመኝ ያስታውሰኛል :: በብላቴናነት ዘመኔ ፥ የሰፈራችን ኗሪዎች ፥ የገና በአል መዋጮ ሰብስበው ፥ ፍሪዳ ጥለው ይቀራመታሉ፤ የተረፈው ተደግሶ ከተበላ ከተጠጣ በሁዋላ፥ ታዳሚዎች ስእለት ማቅረብ ይጀምራሉ::

መጀመርያ የበውቄ አባት ጋሽ ስዩም ተነሱ: :

“በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ከፍሪዳው በፊት እምንቃመሳት አንድ ጠቦት ፍየል አስገባለሁ”

እልልልል!

ጨብጨብ

ቀጥለው የመዋእለ ህጻናት መምህርት ወይዘሮ እታገኝ ተነሱና “በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ፥ አንድ ጥዋ የስጋ ማባያ ድቁስ አቀርባለሁ”

አነስ ያለ ፥ የተድበሰበሰ ጭብጨባ ተሰማ::

በማስከተል፥ የሰፈሩ ጋሪ ነጂ ጋሽ በላይ ብድግ አለና ለሁለት ደቂቃ ሳይናገር ዝም ብሎ ተገተረ፤ ከዝያ ከእንቅልፉ እንደመባነን አለና” በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ …ደስ ይለኛል “ አለና ተቀመጠ::

እድምተኛው አጉረመረመ::

መጨረሻ ወይዘሮ ማሚት ተነሱ፤ ሻሻቸውን ነጠላቸውን አስተካከሉ፤ ጠላ የረጠበውን ያፋቸውን ጠርዝ ጠራረጉ ፤

“ በሚቀጥለው አመት ፤ ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ፥ አንድ ጋን ጠጅ ...”

እድርተኛው አላስጨረሳቸውም ፤ እስከ ሰላሌ የሚሰማ ጭብጨባ ወረደ! ደን ጠባቂው አቶ ቢረሳውማ ነሽጦት ብድግ አለና ፥ ከ”ነጻ ርምጃ ወዲህ “ ተተኩሶ የማያውቀውን አብራራው ጠመንጃውን ወደ ሰማይ ደግኖ ሁለት ጥይት ለቀቀ! በጭብጨባው እና በተኩሱ መሀል ወይዘሮ ማሚት “ አስጨርሱኛ ! “ ሲሉ እሰማለሁ::

ጭብጨባው በረድ ሲል ፥ የባሩዱ መአዛ ገልል ሲል ፥ ማሚት እንዲህ አሉ፤

“ በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ አንድ ጋን ጠጅ የሚያስንቅ ፤ ማንቆርቆርያ ሙሉ ጠላ አቀርባለሁ”: :


ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.7K viewsAbela, 05:50
Open / Comment
2023-03-21 00:03:29
ጥያቄ 44: ፍየሏ በየትኛው ገመድ ነው የታሰረችው?

#_መልሳችሁን ቁጥር በመጫን ይመልሱ
82 viewspetelare Stay true, 21:03
Open / Comment
2023-03-20 23:57:05
የናንተ ኮከቦ ምንድ ነው
211 viewspetelare Stay true, 20:57
Open / Comment
2023-03-20 20:25:06 ክፍል ፭

"....መፈቀር ሁሉም ሊያገኘው የማይችል ፀጋ ነው"

"ደስ ይላል የምር በእናትህ ቀጥል"

"እስኪ የምንኖርበትን ምክንያት ከማየት እንጀምር ለምንድን ነው?ለማን ነው? የምንኖረው ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው ምላሽ ምንድን ነው? ለሆነ ሰው አይደል? ለምንወደው፣ለምናስብለት፣ለምናፈቅረው፣ የኛ መኖር ግድ ለሚሰጠው ፣ ለሚያስደስተው ፣ለሚፈልገን ፣ለምናስፈልገው... መውደድ በቃ ራስሽን አሳልፈሽ ለወደድሽው ሰው መስጠት ነው ብየ አስባለሁ በነገራችን ላይ ራስን አሳልፎ መስጠት ስልሽ መሞት ማለቴ አደለም ዋጋ እንደምትሰጭው ማሳየት ማለት ነው በተለያየ መንገድ ለምሳሌ ብዙ ጊዜሽን ከዛ ሰው ጋር ማሳለፍ።መቼም ከማትፈልጊው ሰው ጋር አንድ ደቂቃ እንኳ ብትሆን ማሳለፉ ይከብድሻል ከአንዳንዶቹ ጋር ደግሞ የፈለግሽውን ያህል ጊዜ አብረሻቸው ብታሳልፊ እንኳ ውስጥሽን የሚሰማሽ አንዳች ደስ የሚል ስሜት አለ። እሱን ስሜት ነው ለእኔ መውደድ የምለው ፍቅር ሲሆን ግን መስዋዕትነቱም ስሜቱም የበለጠ ከፍ ይላል አለ አደል በጣም በጣም መውደድሽ ይበዛና ስስት ያስጀምርሻል ሌላ ባላየው ትያለሽ ፤ ከሌላ ጋር ባያወራ ትመኛለሽ፤ከሌላ ጋር ባይሳሳቅ ባይጫወት ትመኛለሽ ፤ ብቻሽን ከዚህ ሰው ጋር ብትጠፊ ከዚች አለም ላይ አንድም የሚጎልብሽ ነገር እንደሌለ ይሰማሻል፤የሁሉ ነገርሽ መለኪያ እሱ ይሆናል።ፍቅር ውስጥ ሁሉም ነገሮች ከተፈቃሪው በታች ይሆናሉ። ሀገር ከእሱ አንፃር ተራ አፈር ትሆንብሻለች፤ ቤተሰቦችሽ ከእሱ አንፃር ምንም ስሜት የማይሰጡ የግለሰቦች ጥርቅም ይሆኑብሻል ፤ ምግብ እና እንቅልፍ ላንቺ ቅንጦት ይመስሉሻል ፤ ጎደለኝ የምትይውን ነገር ሁሉ በዚህ ሰው ትደፍኝዋለሽና። ፍቅር ሙሉነት ነው! በተፋቀሩ ሰወች መሀል ክፍት ቦታ አይኖርም።ፍቅር የማያልፈው መሰናክል፣ የማይዘለው ዝላይ፣ የማይስተው ጦር አይኖርም። ጣፋጭ ነው! ይስባል፣ ያጓጓል ግን ደግሞ በዛውም ልክ ያማል የፍቅር ህመም ግን ከሌሎቹ የሚለየው ህመሙ ራሱ መፈቀሩ ነው። መናፈቁ ህመም ፣ ተቃጥሮ መጠበቁ ህመም ፣ ቻው ተባብሎ መለያየቱ ህመም ህመም ህመም ህመም... ግን ያለእነዚህ ህመሞች ፍቅር ምንም ነው ምንም! የምታፈቅሪውን ሰው ስትናፍቂው ነው የበለጠ ምን ያህል እንደምትወጂው የሚገባሽ ከዛ በኋላ ህልምሽን ማጋራት ትጀምሪያለሽ ምንም የምትሰስችው ነገር አይኖርሽም ለዛ ሰው። ጊዜሽን ገንዘብሽን ሀሳብሽን ፍቅርሽን አካልሽን ምንም ነገርሽን ከዛ ሰው መደበቅ አይሆንልሽም ያ ተፈቃሪ እጅ ወደላይ አስብሎሻልና ምንምሽን ከዛ ቁጥጥር ማራቅ አትችይም እጅ ወደላይ የተባልሽበት መሳሪያው ፍቅር ስለሆነ..."

"እስኪ እንደውም በዛው ስለ ፍቅር ሕይወትህ አጫውተኝ ነግረኸኝ አታውቅምኮ" ሁኔታው ቅይርይር አለ ደህና የነበረው ፊቱ ባንዴው ጠወለገ
"ይቅርታ ማንሳት የማትፈልገውን ጉዳይ አነሳሁ መሰለኝ"

"አይ ችግር የለውም"

"እና ትነግረኛለህ?"

"ስለ ምኑ?"

"ስለ ፍቅር ሕ..."

"የለኝም"

"ስለበፊቷምኮ ሊሆን ይችላል..." ጮክ ብሎ አቋረጠኝና
"የበፊቷ አደለችም። የበፊቷ ፣ የድሮዋ ሲሉብኝ አልወድም" ደነገጥኩ ለረጅም ደቂቃ ዝም ተባባልን ምን ብየ ጨዋታ መቀየር እንዳለብኝ እያሰብኩ እያለ መናገር ጀመረ...

"ከልጅነታችን ጀምሮ በሚያስብል መልኩ አብረን ነው ያደግነው።ሁሌም ትምህርት ቤት የምሄደውም የምመለሰውም ከእሷ ጋር ነበር ቤቷ አስገብቻት ነበር መንገዴን የምቀጥለው ቤታቸውም ቢሆን ለኔ እንግዳየ አልነበረም ገብቼ እጫወት ነበር ወላጆቿም ቢሆኑ ይወዱኝ ነበር ለረጅም አመት እንደ እህቴ ነበረ የማያት 9ኛ ክፍል አካባቢ ስንደርስ ግን የተለየ ስሜት ይሰማኝ ጀመር በእህትነት አይን ብቻ ማየትን አልችል አልኩ። ይባስ ብሎ ደግሞ እሷ ላይ ሙሉ ውበትን ደፋባት።አይኗን ማየት ከእሳት በላይ የሚያቃጥል ጨረር ሆኖ ልቤን ያርደው ጀመር። ከጎኗ ሆኜ እያደገች፣እያማረች፣ እየተዋበች ፣እየፈካች ስትሄድ መታዘብ ሆነ ስራየ።ሙቀቷ አቃጠለኝ አሳሳችኝ! ሳሳሁላት። ከአይኔ እንዳትጠፋ መጠንቀቅ አበዛሁ ጎኔ ካልሆነች እየናፈቀችኝ ተቸገርኩ። ለረጅም ጊዜ የእህትነት ነው እያልኩ ራሴን ላታልለው ብሞክርም ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ። እንደፈለግኩ አወራትና አጫውታት የነበርኩት ልጅ አይኗን ሳይ ማፈር ጀመርኩ። ብቻየን መብሰልሰሌ ባሰና ዝምታ አበዛሁ።አንድ ቀን ግን ወሰንኩ። የተሰማኝን ልተነፍስላት ፤ ወደድኩሽ ልላት ፤ ልጽፍላት። ሁለት ሶስቴ ማሰብ ሳያስፈልገኝ በጥንቃቄ ባንዴው ፃፍኩት ነገር ግን ሌላ ስጋት ደርሶ ተደቀነብኝ ስነግራት አልፈልግም ፤ ከዚ በኋላ አታውቀኝም አላውቅህም ብትለኝስ አይኗን ሳላይ መዋሉን እንዴት እችለዋለሁ?እንዲሁ ፀጥ ብየ ከጎኗ ሆኜ ድምፄን አጥፍቼ ባፈቅራት ይሻላል የሚለው ሙግት አስቸገረኝ። ነገር ግን እኔ አፍኜው በጭንቀት ከምፈነዳ የመጣው ይምጣ ብየ ልገላገለው ወሰንኩ ከዛ በማግስቱ...." አለና አየር ወሰደ ታሪኩን ሲናገር ፊቱ ላይ በግልፅ የሚነበቡ ስሜቶች ይፈራረቃሉ ሁኔታው አጠገቡ ላለሁት ለእኔ ሳይሆን ለአምላኩ ወይም ለራሱ የሚተርክ ይመስላል

"..ከዛ በማግስቱ በቦርሳዋ ኪስ ላስቀምጥላት ወስኜ የፃፍኩትን በጥንቃቄ አጥፌ አዘጋጀሁና የእረፍት ሰአትን መጠባበቅ ጀመርኩ። ልክ እረፍት ስንወጣ አብሬአት ትንሽ ቆየሁና 'ቆይ መጣሁ' ብያት ወደክፍል ተመለስኩ የቦርሳዋን ትንሹን ክፍል ከፍቼ የጻፍኩትን ላስቀምጥ ስል በተመሳሳይ መልኩ የታጠፈ ወረቀት ተቀምጦ አገኘሁ። እጢየ ዱብ አለ አልቅስ አልቅስ አሰኘኝ የተቀደምኩ እንደሆነ ተሰማኝ ቦርሳዋን እንደነበረ ዘግቼ ምንም እንዳልተፈጠረ ልመለስ ስል ደግሞ አንዳች የልቤ ክፍል 'ቦርሳው ውስጥ ያለው ወረቀት እንደታጠፈ ነው ስለዚህ አላነበበችውም ማለት ነው እሱን አውጣና ያንተን አስቀምጠው' አለኝ ይሄኛው ሀሳቤም አሸነፈና ቦርሳዋ ውስጥ ያገኘሁትን ወረቀት አውጥቼ በኪሴ ይዤ የኔን ወረቀት ቦርሳዋ ውስጥ አርጌ እየሮጥኩ ወደእሷ ተመለስኩ። እስካሁን ስሟን አልነገርኩሽም አይደል ሪታ! ሪታ ትባላለች አይ እሷ! ቆንጆ ነበረች ቆንጆ የሚለው ከበቃት ክብ ፊቷ ላይ ፈጣሪ ጥበቤን አዩልኝ እያለ ያስቀመጣቸው የሚመስሉ አይኖቿ፣ ከንፈሯ ፣ ቀጥ ያለው አፍንጫዋ ብቻ ምን ልበልሽ በቃ ልቅም ያለች ቆንጆ። እና የዛን ቀን ያንን ወረቀት በእጄ ካስገባሁ በኋላ ቀኑን ሙሉ ሳስበው የነበረው ቤት ገብቼ ማን አባቱ ሊነጥቀኝ እንደነበረ አውቄ ለዚህ ሀሳቡ እንዴት አርጌ ልኩን እንደማሳየው ነበር። የቀኑ ትምህርት ሲያልቅ እንደተለመደው ቤት ካደረስኳት በኋላ ወደቤቴ ሮጥኩ። ወረቀቱን ለማየት ቸኩያለሁ ምኝታ ቤቴ ገብቼ ቦርሳየን ወዲያ ወርውሬ ልብሴን እንኳን ሳልቀይር ወረቀቱን አውጥቼ ማንበብ ጀመርኩ።ልክ ከፍቼ ማንበብ ስጀምር ፈፅሞ ያልጠበቅኩት ነገር ተፈጠረ የራሴን ያህል የማውቀው የእጅ ፅሁፍ የራሴን ያህል የማውቀው የፊደል አጣጣል ከአይኔ ገጠመ። ልቤ ምቷ ሲፈጥን ይታወቀኛል ላምን አልቻልኩም...."


...ይቀጥላል...

በአቤኒ የተጻፈ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.3K viewsAbela, 17:25
Open / Comment
2023-03-20 15:38:38

በማላውቀው ሀገር
ጥሎኚ የማውቀው ሰው ፣

መንገዴን በሙሉ
የውሃ ኑሮ አረገው፣

____

ግዕዝ ሙላት

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.7K viewsAbela, 12:38
Open / Comment
2023-03-20 11:27:28 #እንዲ_ነው_ሚከፈል



ትላንትና ሌሊት ናፍቆትሽ ቀስቅሶኝ አስሬ ስነሳ፣
እንደው የኔ ፍቅር ያየሁት አበሳ፣
አሰኝቶኝ ነበር በካልቾ በጥፊ በመታውሽ ብዬ፣
ዳሩ ምን ያደርጋል ዛሬም አብሬሽ ነኝ መከፋቴን ጥዬ።


እናም...
ቀን ቀንን ሲተካ ሲገባኝ ምስጢሩ እያደር ስረዳው፣
እንዲ ነው ሚከፈል ሰው የማፍቀር እዳው።

#ሄኖክ_ብርሃኑ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.2K viewsAbela, 08:27
Open / Comment
2023-03-20 08:29:09
ሙሉቀን ስትስቁ መዋል ከፈለጋችሁ ቻናላችንን በመቀላቀል በሚለቀቁ ቀልዶች እራሳችሁን አዝናኑ

https://t.me/+Vz-KtBwL5ESTqN4u
https://t.me/+Vz-KtBwL5ESTqN4u
111 viewsErmi , 05:29
Open / Comment
2023-03-20 08:25:27
የጠበሳ ዘዴዎች ለወንድም ለሴትም ሴቶች ደፍረዉ የማይናገሩት ግን ከወንዶች የሚጠብቋቸዉ 7 ነገሮች
OPEN
94 viewsErmi , 05:25
Open / Comment
2023-03-20 08:03:06
#መሪጌታ_መንግስቱ የባህል_ህክምና
በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚኖሩም መምጣት ሳያስፈልግ ባሉበት እንሰራለን 
የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋ 0919525031
1 ለመፍትሄ ሀብት
2 ለህማም
3 ለመስተፋቅር
4 ቡዳ ለበላው
5 ለገበያ
6 የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 ሚስጥር የሚነግር
8 ራዕይ የሚያሳይ
9 ለዓቃቤ ርዕስ
10 ለመክስት
11 ለቀለም(ለትምህርት)
12 ሰላቢ የማያስጠጋ
13 ለመፍትሔ ስራይ
14 ጋኔን ለያዘው ሰው
15 ለሁሉ ሠናይ
16 ለቁራኛ
17 ለአምፅኦ
23 ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ
24 ለግርማ ሞገስ
25 መርበቡተ ሰለሞን
26 ለዓይነ ጥላ
27 ምስሐበ ንዋይ ወምስሐበ ሰብእ
28 ለሁሉ መስተፋቅር
29 ጸሎተ ዕለታት
30 ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
31 ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
32 ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
33 ለድምፅ
34 ለብልት

ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ

1 የመኖሪያ ፍቃድ ላላገኙ  መፍትሄ
2. ከሀገር ውጪ ስራ እድል ላጡ
3. ንግድ ጀምረው አልሳካ ላላቸው
4. ገንዘብ ለሚያባክኑ
5 ሰውፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ 
6. ለሀብት  ለንብረት ሚሆንም አለን
7   ለስንፈተ ወሲብ መፍትሄ ለውጪ ሀገር ለሚኖሩትም እየሰራን ነው
8 ፍቅረኛ አልያዝ ላላቸውም አለን
9. ትምህርት አልገባ ላለው
10 መስተፋቅር ፣የህዝብ መስተፋቅር
11. ከሀገር መውጣት እየፈለጉ ላልተሳካላቸው ። ከሀገር ውጪ ላላችውም መፍትሄ በልዩ ሁኔታ አለን  ይምጡ ይደውሉ ያማክሩን ።
ለምንኛውም ጥያቄዎ ይደዉሉ
0919525031
+251919525031
ባላቹህበት እንሰራለን
92 viewsAbela, 05:03
Open / Comment