Get Mystery Box with random crypto!

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መዓዛ መሃመድና ሰለሞን ሹምዬ በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ወሰነ። የፈደራል | YeneTube

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መዓዛ መሃመድና ሰለሞን ሹምዬ በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ወሰነ።

የፈደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ መዓዛ መሃመድ በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንድትለቀቅ መወሰኑ ይታወሳል።ይሁን እንጂ ፖሊስ በጠየቀው ይግባኝ መሰረት ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተጨማሪ 5 ቀናትን ለፖሊስ መፍቀዱ አይዘነጋም።የጋዜጠኛ መዓዛ መሃመድ ጠበቆች ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ይግባኝ መሰረት ፍርድ ቤቱ በ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ ወስኗል።

በተመሳሳይ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቱ በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጣ የፈቀደለት ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ፖሊስ በጠየቀው ይግባኝ መሰረት ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለፖሊስ የምርመራ ጊዜ ዳግም የ5 ቀን የገከዜ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወቃል።ይሁን እንጂ በጠበቆቹ በኩል በጠየቀው ይግባኝ መሰረት ጠቅላይ ፍ/ቤቱ የታችኛው ፍ/ቤት ውሳኔ ተከብሮ በ10 ሺህ ብር ዋስ እስር እንዲወጣ ወስኗል።በሌላ በኩል ደግሞ የጠበቃ አዲሱ ጌታነህን ጉዳይ የተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በ30 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲወጣ ፈቅዷል።

@YeneTube @FikerAssefa