2021-04-21 23:18:38
የ2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ውሹ ሻምፒዮና ውድድር በድምቀት እንደቀጠለ ነው።
ሚያዚያ 13 / 2013 ዓ/ም
ዛሬ በተካሄዱ የፍጻሜ ውድድሮች ፦
ስፒር በወንድ ፦
ፋሲል አምዴ ከኦሮሚያ ወርቅ ፣ አብዱልመጅድ ሙስጠፋ ከአዲስ አበባ ብር ፣ ጋዲሳ ጀማል ከሐረሪ ነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ስፒር በሴት፦
ትንሳኤ ጌታው ከኦሮሚያ ወርቅ ፣ አደይ ሽመልስ ከአዲስ አበባ ብር ፣ ኢስማ ጀማል ከድሬዳዋ የነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ከጂል በወንድ ፦
ወርቅነህ መኮንን ከአዲስ አበባ ወርቅ ፣ ዮሐንስ አዱኛ ከኦሮሚያ ብር ፣ የሱፍ ዳውድ ከድሬዳዋ የነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ከጂል በሴት፦
ረቂቅ ንጉሴ ከአዲስ አበባ ወርቅ ፣ ብስኩት ጉሉማ ከሀረሪ ብር ፣ ገነት ከበደ ከኦሮሚያ ነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ናንገን በወንድ፦
ዮሴፍ ግርማ ከአዲስ አበባ ወርቅ ፣ ኢብራሂም ሽኩሪ ከኦሮሚያ ብር ፣ ቢላዲን ሻፊ ከሐረሪ ነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ናንገን በሴት፦
መክሊት ጌታቸው ከአዲስ አበባ ወርቅ ፣ አያን አብዱሰላም ከድሬዳዋ ብር ፣ መስከረም መስፍን ከኦሮሚያ የነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ሳንሹ ከ48 ኪ.ግ በታች በሴቶች ፦
ፅዮን ቢንያም ከአዲስ አበባ ወርቅ ፣ ሰሚራ አህመድ ከድሬዳዋ ብር ፣ ንብረቴ እሸቴ ከኦሮሚያ የነሀስ ሜዳሊያ አግኝተዋል ፡፡
ሳንሹ 60 – 65 ኪ.ግ በወንዶች ፦
ፈንዲሼ አህመድ ከሐረሪ ወርቅ ፣ ደረጄ ድሪባ ከኦሮሚያ ብር ፣ ሙባረክ ሸምሱ ከአዲስ አበባ የነሀስ ሜዳሊያ አሸናፊ ሆነው ውድድራቸውን አጠናቀዋል፡፡
በአዳማ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የ2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ውሹ ሻምፒዮና ውድድር ነገ ፍፃሜው ያገኛል ።
729 viewsMiskir Solomon, 20:18