Get Mystery Box with random crypto!

‹‹ከአላህ ባርያዎች ውስጥ ሰዎች አሉ፤ ነቢያትም ሰማእታትም ሳይሆኑ ግና የቂያማ ለት ነብያቱ እና | AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር

‹‹ከአላህ ባርያዎች ውስጥ ሰዎች አሉ፤ ነቢያትም ሰማእታትም ሳይሆኑ ግና የቂያማ ለት ነብያቱ እና ስማእታቱ በነዚህ ሰዎች የክብር ስፍራ ይቀኑባቸዋል።›› አሉ ነቢ ሰዐወ።

‹‹ያ ረሱለሏህ! እነማን ናቸው?›› ሲሉ ሰሓባዎች ጠየቁ።

‹‹እነሱ በአላህ ውዴታ የተዋደዱ ሲሆኑ በመካከላቸውም ዝምድናን ያላሳበቡ ናቸው። በውዴታቸው መካከልም ምንም አይነት የጥቅም ግንኙነት የለም ። ወላሂ! ፊቶቻቸው ብርሀን ነው፣ የተሰየሙበት ዙፋንም ብርሀን ነው፣ ቂያማ ለት ሰዉ ሲሸበር እነሡ አይሸበሩም፣ ሰዉ ሲያዝንም በዝያ ለት እነሱ አያዝኑም›› ሲሉ ነቢ ሰዐወ መለሱላቸው።

ከዚያም ረሱል ሰዐወ ይህንን የቁርአን አያ አነበቡ፦‹‹ንቁ! የአላህ ወዳጆች በእነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡

(እነሱም) እነዚያ ያመኑትና ይፈሩት የነበሩ ናቸው።ለእነሱ በቅርቢቱ ሕይወትም በመጨረሻይቱም ብስራት አላቸው፤ የአላህ ቃላት መለወጥ የላትም፤ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡›› ሱረቱ ዩኑስ
#ለሌችም_ሼር_ያድርጉ
https://t.me/joinchat/RXYpviFTL70OQdu2