🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 43.22K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 582

2021-02-12 19:47:47 https://p.dw.com/p/3pGtj?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
4.7K viewsDW Amharic, 16:47
Open / Comment
2021-02-12 19:46:17 https://p.dw.com/p/3pHGg?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
4.8K viewsDW Amharic, 16:46
Open / Comment
2021-02-12 19:42:49 https://p.dw.com/p/3pGWx?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
4.7K viewsDW Amharic, 16:42
Open / Comment
2021-02-12 18:25:13
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል በርካታ ሴቶች የመደፈር ጥቃት እንደደረሰባቸው መንግስት ማረጋገጫ ሰጠ። «በክልሉ በሴቶች ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት መፈጸሙን በስፍራው ካለው ግብረኃይላችን መረጃ አግኝንተናል» ሲሉ የሴቶች ሚንስትሯ ፊልሰን አብዱላሂ ትናንት ሐሙስ ምሽት በትዊተር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። የፌዴራሉ መንግስት « ህግ የማስከበር ዘመቻ» ባለው እና ሕወኃት በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ በሴቶች ላይ በተከታታይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ሲደርስባቸው እንደነበር የአይን ምስክሮች ፣ የህክምና ባለሞያዎች እና የረዲኤት ሰራተኞች ሲያስታውቁ ቆይተዋል። በመንግስት በኩል ለደረሰው ጥቃት እውቅና ሲሰጥ የሚንስትር ፊልሰን አብዱላሂ የመጀመርያው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ሰሞኑን እንዳስታወቀው በትግራይ 108 የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶች መፈጸማቸውን አረጋግጧል። ከእነዚህም ውስጥ ግማሽ ያህሉ በክልሉ መዲና የመቀሌ ከተማ በሁለት ወር ውስጥ የተፈጸመ እንደነበር ገልጿል። ከፊሎቹ ተጠቂዎች ጥቃቱን ያደሩሳበቸው የፌዴራል መንግስቱ ወታደሮች እና አጋሮቻቸው እንደሆኑ ቢገልጹም የጥቃት አድራሾችን ብዛት ከገለልተኛ ወገን ማጣራት አለመቻሉን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እንደሚለው የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ሪፖርት ያልተደረገባቸው አካባቢዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል አመልክቷል።መንግስት ጾታዊ ጥቃትን እንደማይታገስ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል።
ፎቶ/የኢትዮጵያ ሴቶች ሚንስትር
4.9K viewsDW Amharic, 15:25
Open / Comment
2021-02-12 16:20:36
አጣሪ ጉባኤው ባለፉት 5 ዓመታት 14 ጉዳዮችን ብቻ ተመለክቷል!
ህብረተሰቡ የህገመንግስት ትርጉም የሚስፈልጋቸውን ጥያቄዎች ባግባቡ መገንዘብ ባለመቻሉ ባለፉት 5 ዓመታት የቀረቡ አቤቱታዎች በጣም ዝቅተኛ መሆናቸውን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡
የፍርድ ቤቱ ፕረዚደንትና የአማራ ክልል ህገመንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሰብሳቢ አቶ አብዬ ካሳሁን ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ከ2008 ዓ ም ጀምሮ 14 ብቻ የህገ መንግስት ትርጉም አቤቱታዎች ቀርበዋል፡፡
ከዚህ ውስጥ 4ቱ የህገ መንግስት ትርጉም የሚያስፈልጋቸው አቤቱታዎች ሆነው በመገኘታቸው በውሳኔ ሀሳብ በማስደገፍ ለመጨረሻ ውሳኔ ለአማራ ክልል ህገመንግስት ተርጓሚ ኮሚሽን ተልከው የህገ መንግስት ትርጉም ያስፈልጋቸዋል በሚል እንዲፀኑ መደረጉንም አቶ አብዬ ተናግረዋል፡፡
10ሩ ደግሞ እንደማያስፈልጋቸው የውሳኔ ሀሳብ እንደቀረበባቸውም አስረድተዋል፡፡ የአቤቱታዎቹ ቁጥር አናሳነት ችግር አለመኖሩን የሚያሳዩ እንዳልሆነ ያመለከቱት ፕረዚደንቱ፣ በየደረጃው የህገመንግስት ትርጉም የሚሹ ኢ ህገመንግስታዊ ህጎች፣ የተዛቡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችና የፍርድ ቤት ዳኝነቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ መብቱን ወደ ህገመንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አቤት ማለት አለባቸው ሲሉ አመልክተዋል፡፡
በአጠቃላይ በክልሉ ካለው የህዝብ ቁጥር አኳያ የህገመንግስት ትርጉም አቤቱታዎች በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘታቸው ህብረተሰቡ ስለጉዳዩ ግንዛቤ እንደሌለው ማሳያ መሆኑን የገለፁት አቶ አብዬ፣ የህግ አዋቂዎች፣ ብዙሀን መገናኛና የህግ ተቋማት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ አሳስበዋል፡፡
አማራ ክልል 11 አባላት ያሉት የህገ መንግስት አጣሪ ጉበኤ አሉት፡፡
5.1K viewsDW Amharic, 13:20
Open / Comment
2021-02-12 16:19:16
የአውሮጳ ህብረት ማዕቀብ የሚጥልባት ከሆነ ግንኙነቷን ልታቋርጥ እንደምትችል ሩስያ አስጠነቀቀች። ሩስያ ማስጠንቀቂያውን የሰጠችው ምዕራባውያኑ በአሌክስ ናቫልኒ መታሰር በሩስያ ላይ ማዕቀብ ከጣሉ ሩስያ ከሕብረቱ ጋር የሚኖራትን ግንኙነት ልታቋርጥ እንደምትችል የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ስርጌይ ላቭሮቭ ተናግረዋል። ላቭሮቭ ዛሬ በቴሌግራም በሚተላለፍ አንድ ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ «ከሕብረቱ ጋር ግንኙነት ታቋርጡ ይሆን» ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱ »ሕብረቱ የሩስያን ኢኮኖሚ ሊጎዳ የሚችል የማዕቀብ እርምጃ ከወሰደ ሩስያም በበኩሏ የራሷን እርምጃ ትወስዳለች » ሲሉ ተደምጠዋል። « ለዚያ ደግሞ ዝግጁ መሆናችንን እንቀጥላለን» ብለዋል ላቭሮቭ ፡፡ ከዓለማቀፍ ግንኙነት ራሳችንን መነጠል አንፈልግም ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ «ነገር ግን ለዚያ ዝግጁ መሆን ይኖርብናል ፤ «ሰላም ከፈለክ ለጦርነት ተዘጋጅ» የሚል አባባል ለንግግራቸው ተጠቅመዋል፡፡የህብረቱ አንድ ከፍተኛ ባለስልጣን በበኩላቸው ሩስያ ለብቻዋ ለመነጠል እና ምዕራባውያንን ለመከፋፈል እየጣረች ነው ሲሉ ወቅሰዋል። በአውሮፓ ህብረት የሩሲያ ተወካይ ቭላድሚር ቺዝሆቭ ቀደም ሲል ዛሬ አርብ ጥዋት በኢዝቬሺያ ጋዜጣ ላይ በተለይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ የሩሲያ እና የአውሮፓ ህብረት ውይይቶች እንደሚቀጥሉ እና የቦረል ወደ ሞስኮ ለመጓዝ ፈቃደኛ መሆናቸው ነገሮች መስመር እንዳይለቁ ለማድረግ የሚያስችል ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥራል ብለዋል ፡፡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ጀርመን እና ፈረንሳይ ይሁንታቸውን ከሰጡ በኋላ የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አጋሮች ላይ የጉዞ እቀባ እና የንብረት እገዳ ለመጣል አቅዷል ፡፡
4.3K viewsDW Amharic, 13:19
Open / Comment
2021-02-12 16:18:36 በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር የተፈጠረውን ውጥረት በውይይት መፍታት እንደሚገባ የሁለቱ አገሮች ምሁራን ገለጡ፡፡ ከሱዳን የመጡና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምሁራን በባሕር ዳር ባደረጉት ውይይት የተፈጠረውን የድንበር ጉዳይ በጦርነት መፍታት ዘላቂ መፍትሔ የለውም ብለዋል። ለመፍትሄው ውይይት ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ታሪክ ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር አይቸግረው አደራ እንዳሉት የድንበር ጉዳይ የሁለቱ አገሮች ችግር ብቻ እንዳልሆነ አስታውሰዋል ። ቅኝ ገዥዎች የፈጠሩት ችግር የብዙ አፍሪካ አገሮች ተግዳሮትና የግጭት ምንጭ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሶስተኛ ዲግሪያቸውን በኢትዮ ሱዳን ድንበር ጉዳይ ላይ የሰሩት በወሎ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና ቅርስ አስተዳደር መምህር ዶ/ር ዓለማየሁ እርቅይሁን በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ችግር በውይይት መፈታት አለበት፣ ያ የሚሆነው ግን ሱዳን ወደነበረችበት ስትመለስ ብቻ ነው ብለዋል፡፡ በሱዳን ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የስነጥበብ ፕሮፌሰር ዶ/ር ኡመር አላሚን በበኩላቸው ሁለቱም አገሮች ህዝቦቻቸውን ወዳልተገባ ሁኔታ የሚወስዱ ሽፍቶችን ማስወገድ አለባቸው ሲሉ ለዶይቼ ቬከ ገልፀዋል፡፡
4.2K viewsDW Amharic, 13:18
Open / Comment
2021-02-12 16:17:30
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የተደረገው ጦርነት በርካታ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ማስከተሉ ሲነገር ቆይቷል። ጦርነቱን ተከትሎ ከደረሰው የህይወት እና የአካል ጉዳት ባሻገር የዜጎች ከመኖርያ ቄዬአቸው መፈናቀላቸው እና በርካታ ማሕበራዊ ችግሮች መፈጠራቸውም እንዲሁ በመንግስትም ሆነ በሌሎች አለማቀፍ የመገናኛ ብዙኃን እና ተቋማት በኩል መረጃዎች ሲወጡ ቆይቷል። በትግራይ ክልል ከተፈጠረው ቀውስ ባሻገር በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚደርሱ ሰብአዊ እና ሌሎች ፖለቲካዊ አንድምታ ያላቸው አለመረጋጋቶችን በተመለከተ ከመንግስትም ሆነ ከሌሎች አካላት የሚወጡ መረጃዎች ሚዛናቸውን ያልጠበቁ ስለመሆኑ ሲነገር ይሰማል። በትግራይ ክልል የተከሰተውን ቀውስንም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚደርሱ ሰብአዊ ችግሮች በመንግስት ፣ በሌሎች የአለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና የረድኤት ድርጅቶች የሚወጡ መረጃዎች ምን ያህል ሚዛናቸውን የጠበቁ ናቸው? እርስ በእርሳቸው የተጣረሱ መረጃዎች እንዲወጡ ምክንያቱ ምን ይሆን የዜጎች ትክክለኛ መረጃን ከማግኘት መብት እና ከወገንተኝነት የጸዳ እና ትክክለኛ መረጃ ከማግኘት አንጻር ምን መደረግ አለበትስ ትላላችሁ? ሀሳባችሁን አካፍሉን።
7.1K viewsDW Amharic, 13:17
Open / Comment
2021-02-12 13:33:19 https://p.dw.com/p/3pGEt?maca=amh-Facebook-dw
5.3K viewsDW Amharic, 10:33
Open / Comment
2021-02-11 20:41:20 በአዲስ አበባ የእናቶች ሆስፒታል ምርቃት

በአይነቱ ልዩ እና በርካታ መስፈርቶችን ያሟላ ነው የተባለ የእናቶችና የሕጻናት ሆስፒታል ዛሬ በአዲስ አበባ ተመረቀ። በክቡር ዶክተር አበበች ጎበና ስም የተሰየመው ሀኪም ቤት በአዲስ አበባ አያት ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ነው ለአገልግሎት ክፍት የሆነው።
https://p.dw.com/p/3pEQ3?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
6.4K viewsDW Amharic, 17:41
Open / Comment