🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ግጥም በድምፅ

Logo of telegram channel audio_poems — ግጥም በድምፅ
Logo of telegram channel audio_poems — ግጥም በድምፅ
Channel address: @audio_poems
Categories: Uncategorized
Language: English
Subscribers: 10.47K
Description from channel

@Air_me1 ግጥሞን በዚ ይላኩ

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


The latest Messages 8

2023-03-12 22:36:10 በርግጥ በኔ ዘመን ....................

እምነት እንደ ጉሊት ሲቸበቸብ ያድራል
ቃል አክባሪ ግትር ተብሎ ይወቀሳል::

እዎ በኔ ዘመን......................

ፍቅር ከጭን ዳሌ ውሉን ያሳሰረ
የገበያው ዘዴ ሳይለዩ መግዛትን ብሂል የሰበረ::

በፍቅር ቅኝት ስም ሴሰኝነት ነግሶ
የነፍስ ፍቃዷ ተድሶ

በየ ጥጋ ጥጉ አስክሮ ሚያዳራ
ሺህ ጭኖችን ታቅፎ ሺህ ነፍስ የሚያሳጣ
የዘመናት ዋጋ.......
ወጣትነት ልኩ.........

መዝናናት ታቅፎ ውስጡ እዥ ያዘለ
በፈረሰ ደስታ ጠማማ ምሰሶ ታቅፎ የዋለ::

የእድሜ ጣሪያ ልስን
በእኔ ከሞትኩ ሰርዶ
በሺ አይኖር ወርዶ
በውሽት ቅብ ውበት ከላይ የተዋበ
አራዳ የሚያስብል አንዳንድ ስግጥና እለ::

በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ

@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
163 viewsTIZITA21, 19:36
Open / Comment
2023-03-12 08:41:11
https://t.me/MyMessagesss
465 viewsBarkot A, 05:41
Open / Comment
2023-03-10 09:43:09
Join

@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
178 viewsEyob Z Mariam, 06:43
Open / Comment
2023-03-09 18:18:36
ምናብ ትመስይኛለሽ
እንደ የቀን ህልሜ
እንደ ደራሽ ፀሎት፣
ፅናቴን ፈትና
እንደረካች እምነት።

ደሞ ስንለወጥ
ጊዜ ሲያይልብን፣
በወጀብ መሀከል
ስንቃዥ ለነብሳችን፣
ምናብ ይመስለኛል
የኖርነው ፍቅራችን
ስሜ 'ሚናፍቀኝ
እንቡጥ ከንፈርሽን፤

ግን አለሁ፥
ዛሬም  እንደተከዝኩኝ
ምናብሽን እንዳደንኩኝ
(ግን አለሁ)
ትዝታሽን ተደግፌ
ከህይወትሽ ተሸርፌ
ናፍቆትሽን ለዕቅፌ
(ግን አለሁ)
ፈገግታሽን ተንተርሼ
መዓዛሽን ተፈውሼ
(ግን አለሁ)
ያች ቦታ ስጠብቅሽ
ምናብ ይመስለኛል
የሰማሁት ድምፅሽ።

https://t.me/MyMessagesss
476 viewsBarkot A, 15:18
Open / Comment
2023-03-08 23:13:20 አገባህ ነበረ……………

ቆሎ 'የቆረጠምን እኖራለን ውዴ
ልጅ በልጅ ይሆናል ቤታችን መውደዴ
አንቺ ውሀ አጣጬ የእግዜር ባለ አደራ
እሺ በይኝ ላግብሽ ፍቅራችንም ይድራ::

አለኝ የኔ ሚስኪን..............
አገባህ ነበረ..................

ቆሎ ባልቆረጥም እርሀብ ባይደፋኝ
ሊያውም በዚ ዘመን..........

ቆሎ ያልከው ውዴ
ዝም ብለህ ስታየኝ የኤርፎራ ዶሮ እመስላለሁ እንዴ?

ጭራሹን.................

ልጅ በልጅ ሆኜልህ
አንዱን ከኃላዬ ሌላውን ከፊቴ
ገሚሱን በግራ ገሚሱን በቀኜ
እሪ እምቧ ሲሉብኝ መንምኜ መንምኜ

የድስት ፍቅፋቂ በጋራ ስንበላ
ጎረቤት ቢረበሽ ይደብራል ኃላ

እኔም ተማርሬ እግዜር ከሚከፋዉ
ቆሎህን ለብቻህ ተደብቅህ ብላው::


በትዝታ ወልዴ እንደተፃፈ

@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
@Tizitawolde_poems
129 viewsTIZITA21, 20:13
Open / Comment
2023-03-08 06:27:58 ይህን መልዕክት ለምቶዷቸው ሴቶች ላኩ

ይህ የደረሰሽ ሴት ደግሞ ላኪው አጥብቆ ይወድሻል



በሴቶች ቀን እንዲ ልባርካቹ


ምሳ=29:-10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።

11 የባልዋ ልብ ይታመንባታል። ምርኮም አይጐድልበትም።

12 ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም።

13 የበግ ጠጕርና የተልባ እግር ትፈልጋለች፥ በእጆችዋም ደስ ብሎአት ትሠራለች።

14 እርስዋ እንደ ነጋዴ መርከብ ናት፤ ከሩቅ አገር ምግብዋን ትሰበስባለች።

15 ገና ሌሊት ሳለ ትነሣለች ለቤትዋም ሰዎች ምግባቸውን፥ ለገረዶችዋም ተግባራቸውን ትሰጣለች።

16 እርሻንም ተመልክታ ትገዛለች፤ ከእጅዋም ፍሬ ወይን ትተክላለች።

17 ወገብዋን በኃይል ትታጠቃለች፥ ክንድዋንም ታበረታለች።

18 ንግድዋ መልካም እንደ ሆነ ትመለከታለች፤ መብራትዋ በሌሊት አይጠፋም።

19 እጅዋን ወደ አመልማሎ ትዘረጋለች፥ ጣቶችዋም እንዝርትን ይይዛሉ።

20 እጅዋን ወደ ድሀ ትዘረጋለች፥ ወደ ችግረኛም እጅዋን ትሰድዳለች።

21 ለቤትዋ ሰዎች ከበረዶ ብርድ የተነሣ አትፈራም፥ የቤትዋ ሰዎች ሁሉ እጥፍ ድርብ የለበሱ ናቸውና።

22 ለራስዋም ግብረ መርፌ ስጋጃ ትሠራለች ጥሩ በፍታና ቀይ ግምጃ ትለብሳለች።

23 ባልዋ በአገር ሽማግሌዎች መካከል በሸንጎ በተቀመጠ ጊዜ በበር የታወቀ ይሆናል።

24 የበፍታ ቀሚስ እየሠራች ትሸጣለች፥ ለነጋዴም ድግ ትሸጣለች።

25 ብርታትና ከበሬታ ልብስዋ ነው፤ በኋላም ዘመን ላይ ትስቃለች።

26 አፍዋን በጥበብ ትከፍታለች፤ የርኅራኄም ሕግ በምላስዋ አለ።

27 የቤትዋንም ሰዎች አካሄድ በደኅና ትመለከታለች፥ የሀኬትንም እንጀራ አትበላም።

28 ልጆችዋ ይነሣሉ፥ ምስጋናዋንም ይናገራሉ፤ ባልዋ ደግሞ እንዲህ ብሎ ያመሰግናታል።

29 መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ፥ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ።

30 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።

31 ከእጅዋ ፍሬ ስጡአት፥ ሥራዎችዋም በሸንጎ ያመስግኑአት።


ይህ ይሁንላቹ

https://t.me/MyMessagesss
522 viewsBarkot A, 03:27
Open / Comment
2023-03-06 19:39:14
"መሰከረም" ላይ
.
.
በጋ ሲሆን ገና፤
አውልቆ ለመጣል የወበቁን ድባት፣
ነፍሴን ለማለምለም ፍቅር ለመጋራት፣
ቃል እየወለድኩኝ፤
ቀን እየማለድኩኝ፤
ፍቅሬን "ነይ" አልልም፡፡
ለሙቀት ሳልሰጋ፤
ወረተኛው በጋ፤
እኔን ሳያማክር እንደመጣ ያልፋል፣
ክረምት አስከትሎ ከፊት ይሰለፋል፡፡
.
.
ቁር እየወለደ፤
ብርዱ ሲደራረብ በክረምቱ ወራት፣
ፍቅር ብትጠማ ነፍሴን ሰው ቢርባት፡፡
ውርጩን ስረፈራሁ ጣፋጯን በማለም፣
ቃል እያሰማመርኩ ፍቅሬን "ነይ" አልልም፡፡

በወፍ ጎጆዬ ውስጥ፤
በወፍራም ሹራብ ላይ ካቦርቴን ደርቤ፣
ቦት ተጫምቼ፤
ጋቢ ወይ ብልኮ አንዱን ተከንቤ፡፡
ሸንቁር ምድጃ ላይ፤
እሳት አያይዤ እሸት እየጠበስኩ፣
ውርጩን እያሟሸሁ ብርዱን እየሰበርኩ፣
~ክረምቴን አልፋለው፣
ለሊት በህልም አክናፍ፤
ካንዱ ምዕዋር ላይ ሙቀት እቀዝፋለዉ፡፡

ይልቅ፤
በዘመን ማለዳ፤
በፀደይ ተወልዳ፤
ደመናው ተንዶ ጀምበሯ ስትወጣ፣
እንደ መልካም እድል፤
እንደ መስቀሏ ወፍ ባ'ደይ ተንቆጥቁጣ፣
ያምላኬ ስጦታ፤
የምወዳት ፍቅሬ "መስከረም" ላይ ትምጣ፡፡

ትምጣ ትዝታዬ፤
ታሽረኝ ከመድከም፤
ዝለቴን ታክመው ተሽጣ ከጎኔ፤
የናፈቁት ገላ "እቅፍ" ሲያረጉት ፋሲካ ነው ያኔ፡፡

ዐብይ


https://t.me/MyMessagesss
349 viewsBarkot A, 16:39
Open / Comment
2023-03-06 09:11:12
ምንድነሽ ምንድነኝ ?

Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
516 viewsEyob Z Mariam, 06:11
Open / Comment
2023-03-05 09:36:48
አንቺ


( ዮሐንስ ሀብተማሪያም )


ደህናይቱ!!!
መልካሚቱ!!!

አንቺ!!!

የጅምሬ መሰረቱ፡፡

የቀኝ መዋያ ልኬቱ
የደግ እጣዬ ድምቀቱ፡፡

የቀልብያዬ ስሪቱ
መንፈላሰሻ ምቾቱ፡፡

መታመኛዬ መቅደሴ
ሕያው መኖሪያ ለነፍሴ፡፡

ቅኔ ማኅሌት ለያሬድ
ታላቅ ቅዳሴ ለኤፍሬም

ፅና መስቀሉ ለአማኝ
እጣን ከርቤው ነሽ ለዓለም፡፡

እስከዘላለም ዘላም
ለዘለዓለም አሜኑ

የሩሔ ረቂቅ ስምረቱ
ነግሶ ፃድቅም መሆኑ፡፡

ደህናይቱ!!!
መልካሚቱ!!!

አንቺዪቱ!!!!

የቀን ሰመመን ስፍሬ
መፈላሰፊያ ቀመሬ።

በሐቁ ወገን መኖሬ
በቅኑ መጠጥ ስካሬ፡፡

የኔ እኔነት ፍካሬ
ሁላ ሁሉዬ ለፍቅሬ
ዘላለማዊ መስመሬ፡፡

አንቺ!!!

ሰማያዊ ዳስ ላ'ብርሐም
የመስተንግዶው ማሕተም፡፡

ከምድር ሰማይ መሰላል
የቃል ኪዳኔ ልዪ ቃል፡፡

እንደርግብ ላባ ለስላሳ
የዋህነትሽ ግሪሳ፡፡

ያንበሳ ጉፈር ግርማዊት
ዥንጉርጉር ቀለም ነብራዊት
የማትለ'ቂ ኢትዮጵያዊት፡፡

አንቺ!!!

ምሬታዊነት መጣፈጥ
በተነኪነት መመሰጥ
ሐቂቃ ኩነት ለመግለጥ፡፡

እኔን ያተጋሽ መሰጠት
ቅኔን የቃኘሽ መለኮት
የመነካቴ አብነት፡፡

ወደመጡበት ለመምጣት
የሄዱበትን ለመሄድ

በሕይወት እውነት መወለድ
ከእውነት ሕይወት መናገድ፡፡

አንቺ!!!
አንቺ!!!

አንቺ ብቻ አንቺ!!!

ምስጢር የምትፈቺ
እኔን የምትረቺ፡፡


https://t.me/MyMessagesss
168 viewsBarkot A, 06:36
Open / Comment
2023-03-02 22:16:38
Join
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
@poeteyobzmariam
186 viewsEyob Z Mariam, 19:16
Open / Comment