ሳጥናኤል ቀፈፈው የመለእክት አለቃ ሳጥናኤል ሲባረር ፥ ሰው የመሆን ፈቃድ እምላክ ሰጥቶት ነበር ፥ ሳጥናኤል ግን ከፋው ፥ ሰው መሆን ቀፈፈው ፥ ጌታን ተማፀነ ፥ ሰው አንዳያደርገው አልቅሶ ለመነ ። ከመንበሩ ቀርቦ ሞገተ ፈጣሪን ፥ ከፍጥረትህ ሁሉ ሰው በጣም ይከፈል ፤ ይሄንን አልችልም ሰውነት ይቀፋል ፤ ሞቶስ መቼ ያርፋል ? የሃጥያቱ ዘር ዘመን ይሻገራል ፤ ፍጹም አይማርም አዳኙን ይክዳል ፣ ስሞ ይሸጠዋል ፣ ሰቅሎ ይገድለዋል ፤ ጥበብ አጥሮት እንጂ ሰይጣንን ያስንቃል ። እባክህ አምላኬ ፥ እኔም ፍጥረትህ ነኝ ፥ ሃጥያቴ በዝቶ ምን ብዳፈርህም ፥ ሰው የመሆን ቅጣት አትጥልብኝም ፥ ብሎ ተቀመጠ ሳጥናኤል ቆረጠ ፥ ሰው መሆንን ጠልቶ ሰይጣንን መረጠ ። ያሬድ ዘ. ካህን መሰከረም -12 / 2014 ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 5.8K viewsBewketu, 17:18