•••☆《እነ አድር ባይ ቤቱ》☆••• ሚኪያስ እንዳለው @mikiendialem እጣረሰው ትዕዛዝ አሻፈረኝ ስለው ጌታው ቁጣ አስነሳ፤ ጭራሽ ዱላ አንስቶ እኔን ሊደበድብ በንዴት አገሳ፤ ፡ . ይቅርታ ይቅርታ መማፀን አበዛሁ፤ እሱን ጌታ አክብሬ ሎሌነትን ገዛሁ፤ ድል መንሳቱ ህልሜን በሽንፈት ነሳው፤ ፡ . ሲፈጠር ከሀረጉ ለገዢነት ብቻ የተፈጠረ አለ፤ እንደኔ አይነት ደሞ ከቅባቱ ስለት ሎሌ የሆነ አለ፤ ብቻ በየፊናው ጀብደኛ እና አሽቃባጭ ፈር እየጠረገ፤ እድሜውን ይኖራል ለሌላው አሲይዞ ጥግ እየፈለገ፤ ፡ . መረታት ተፅፎ ለሞቀለት ሁሉ የሚያሸረግደው፤ ለይምሰሉ ውጦት ሰው መሆኑን ካደው። ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 480 viewsAbela, 05:28