አንቺን እንዲሰጠኝ - ሆንኩኝ አምላክ ለማኝ፤ ጧፍ መባ ገዛሁ - ልሰጠው ከሰማኝ፡፡ አንቺዬ... ፀሎቴን ሳልጨርስ - ብትይ እመጣለሁ፤ እኔ እኮ ሞኝ ነኝ፣ ፈጣሪዬን ትቼ - እጠብቅሻለሁ፡፡ እጠብቅሻለሁ!!! በተገተርኩበት፤ እጠብቅሻለሁ፤ በተፈጠረኩበት፡፡ ጊዜ አይፈራረቅ - አይጮኹም አእዋፍ፤ አንቺን ስጠብቅሽ... ለኮስኩት ጨክኜ - ለስለት እንዲሆን የገዛሁት ጧፍ፡፡ ትመጫለሽ አይደል? (ኤልያስ ሽታሁን) ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 3.6K viewsAbela, 04:51