ከታፈንኩ ኋላ ድፍን ሀገር ታሞ ፣ ሀኪም ሲቸግረው "መድሀኒቴ አንቺ ነሽ" ፥ ስል ማንጎራጉረው አንዴ ላስነጠሰሽ ይማርሽ እያልኩኝ ፣ ስጨነቅ የማድረው ሀገር እያነባ ስላንቺ ሳቅ ቅኔ ፣ የምደረድረው ለምን ይመስልሻል? ።።። ከታፈንኩ ኋላ... የማይ የምሰማው ፣ እየሰቀጠጠኝ ዛቻው እንደ በሶ ፣ እየበጠበጠኝ እንደ ባህር ሞገድ ፣ ፍርሀት እየናጠኝ ዝምታን መርጬ ፣ ጨለማ ሲውጠኝ "ጀግና " ያለኝ ሁላ "ፈሪ አረጉት" ብሎ ፣ ውብ ስሜን ሲያጎድፈው ጊዜ እንደ ምዕራብ ሀገሩን በሙሉ ፣ ፅልመት ሲያስታቅፈው "ዐይኖቿ እንደኮከብ ያበራሉ " የሚል ፣ ግጥም የምፅፈው ለምን ይመስልሻል? ።።። ከታፈንኩ ኋላ ሲቃና መከራ ደም እና ደንባራ መቼም የማይለቃት ፣ አንድ ሀገር መውደዴን የሚያውቁ በሙሉ ፣ ሳያውቁልኝ ጉዴን "ዝመት እንጂ" ሲሉኝ ፣ ከፍቶኝ ማኮርፈው ለምን ይመስልሻል ስጋዬና ነፍሴን ፣ መንፈሴን ሚቀፈው? . . . . ከአንቺ ርቄ ብዘምት እኔም ሀገሬም ነን ፣ የምንሸነፈው ። Belay bekle weya ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 3.3K viewsAbela, edited 11:21