(በእመ ብርሃን...) ====++++==== አንዲት ምስኪን ህጻን የመንገዱን መብራት ቋሚ ተደግፋ ድካም ተጫጭኗት ባልጸና ደረቷ ማስቲካ ሸክፋ ተስፋ በቆረጡ ኩልትፍትፍ ፊደላት ቃል እየሰደረች " በእመ ብርሃን አባት አንዲት ፍሬ ግዛኝ " አትለፈኝ አለች ... በአይኖቿ ገመድ በአንደበቷ እስራት በልጅነቷ ክር በሴትነት ጅማት መሐከል ጠፍንጋኝ እንደምን ልለፋት ? እያቀረቀረች...እያዘነበለች አዛኝቱን ጠርታ ፊጥኝ እያሰረች ልለፍ ቢል እግሬ እንኳ..ህሊናየን በየት ታሳልፈዋለች ? ያለኝን ብሰጥሽ ልታፈላስፊኝ ገፍቼሽ ብባዝን በጸጸት ልትቀስፊኝ በመንገዴ ቆመሽ...አትለፈኝ አትበይ አንቺው አትለፊኝ ! #Da_kiyorna ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 3.7K viewsAbela, 16:38