🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ደብሮኝ ነበር ። ትንሽ አእምሮ እክል የገጠመው ሁለት ብር ስጠኝ እያለ የሚለምን ። ሲያየኝ ደ | በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ

ደብሮኝ ነበር ። ትንሽ አእምሮ እክል የገጠመው ሁለት ብር ስጠኝ እያለ የሚለምን ። ሲያየኝ ደስ የሚለው ሶስት ቀን ካለየኝ ምነው ጠፋ ብሎ ተገርሞ የሚጠይቀኝ ።

ኮስተር ብሎ በዘጠናዎቹ.... ኔሽን ጋዜጣ ላይ እነ አሌክሳንድሮቪች ፣ጤርጥዮስ-ከቫቲካን የፃፉትን ሙግቶች ​። ስነምግባር እና የእግዛብሄር ሃሳብ (Moral value and the idea of God) ያብራራልኛል ።1913- 1960 ድረስ ስለኖረው አልበርት ካሙ ስለ ሃሳብ ነፃነት ገደብ ሊጣልበት እንደማይገባ የተከራከረውን ። ቦንቦሊኖ እንዴት እንደተወደደ ...ጋዴ የሚሉት ጫማ ስለመጥፋቱ

ስለማይወደው Nihilist ቱ ኒቼ ..... ለራሱ mental breakdown የገጠመው ሰውዬ እግዜር የለም አለ እያለ.... ሂሂሂሂ እያለ እየሳቀ ያጣጥልልኛል።

ገሬ ቺክ ይፈራል ። አንድ ቀን "ሴክስ አድርገህ ታቃለህ እንዴ?" አልኩት እንዴት እንደተሽኮረመመ እንደ አስራ ሶስት አመት ልጅ አይነት መሽኮርምም ፊቱ ላይ ረበበ ።

ስለ Sex እና Art ግንኙነት ስለሚዘበዝበው Eroticism and Aesthetics እያብራራ ....ወሲብ አድርገህ ታውቃለህ ስለው በዚህ መጠን መሽኮረመሙ ይገርመኛል

የሆነ ሰሞን ድብርት ክፉኛ እየተላፋኝ ነበር ። ከማንም ጋ የማውራት አምሮት አልነበረኝም። የማውቀው ሰው ሲመጣ ችላ አለኝ እንዳይለኝ መንገድ የምቀይርበት ሰሞን ነበር ።

የሆነ ቀን ማኪያቶ የምንጠጣበት ጥግ ጠርዝ ላይ ተቀምጬ መጣ ። ደና ነህ ገሬ አልኩት እጁን ላከልኝ ሲጨብጥ እጁን ላላ አደርጎ ነው " ጠፋህ እኮ? "አለኝ ።

"አለው" ብዬው የሆነ ቀን እንደድሮ ሳንቀራረብ እሰጠው እንደነበረው አስር ብር ሰጠሁት ።

አየኝ ብሩን አየው ተቀበለኝ ። ሄደ ።

በነጋታው እመንገድ በጠዋት አገኘሁት ። ሲያየኝ ፈገግ ፈገግ አላለም ።

ቀጥታ መጥቶ .....

"ራከኝ እኮ አስቀየምኩ እንዴ ማታ ሳስብ.. ሳስብ .. ሳስብ ... ሳስብ ነበር ። ሌላ እኮ እንዳንተ የሚያዳምጠኝ ማንም የለም ። ጓደኛዬ እኮ አንተ ብቻ ነህ" አለኝ ።

አወራሩ ....ታረቀኝ ። እንደድሮ ጆሮ ስጠኝ ...ብር ሰጥተ አታባረኝ ....ነው
እምለው ሳጣ" እ... አሞኝ ነበር" አልኩት
ጓደኛ አመመኝ ተብሎ ይዘጋል ??

ይቅርታ ገሬ ....

አየህ ገረመው እንደሆነ ስሜ አንተ ነህ የምታስታውሰኝ እኮ" ።
.....ድንግጥ ብሎ "አሁን ተሻለ ግን ? "

በኛ መሳቅ ውስጥ የሚስቁ ሲጎልብን የሚጎልባቸው ሰዎች ካሉን ብቻውን ቀላል አይደለም መሰለኝ!!
Adhanom Mitiku

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19