Get Mystery Box with random crypto!

የአውሮጳ ህብረት ኤርትራ ወታድሮቿን ከትግራይ ክልል እንድታስወጣ አሳሰበ:: ሕብረቱ ከዚሕ ቀደም ቀ | DW Amharic

የአውሮጳ ህብረት ኤርትራ ወታድሮቿን ከትግራይ ክልል እንድታስወጣ አሳሰበ:: ሕብረቱ ከዚሕ ቀደም ቀደም ዩናይትድስቴትስ የስጠችውን ተመሳሳይ ማሳሰቢያ በመደገፍ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ዉስጥ መግባትበአካቢዉ ግጭት እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል ሲል ወቅሷል::የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት <<የኤርትራ ወታደሮችበትግራዩ ጦርነት አልተሳተፉም >> ሲሉ የቀረበባቸውን ክስ በየፊናቸው ሲያስተባብሉ ቆይተዋል:: አሁንም የኤርትራው የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል የአዉሮጳ ሕብረትን ማሳሰቢያ አጣጥለዋል::
የአውሮጳ ህብረት ባወጣው መግለጫ እንዳለው የኤርትራ ወታደሮች ጣልቃ ገብነትን በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት የሚሰጧቸው የማስተባበያ አስተያየቶች እርስበእርሳቸው የሚጣረሱ ናቸዉ ብሏል:: ህብረቱ አያይዞም በትግራይ ክልል እየታየ ያለው ሰብአዊ ቀውስ የተለየ ትኩረት ሊያገኝ ይገባል ብሏልም የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እንዲቀርብ ሁኔታዎችን እንዲያመቻችእና ለሰላማዊ ሰዎች እና ለስደተኞች ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቋል:: የኖርዌያውያን ስደተኞች ጉዳይ ምክር ቤት እንዳለው <<በትግራይ ክልል ኤርትራዉያን ስደተኞች በሠፈሩበት መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ለስደተኞቹ አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ህንጻዎች እና ሌሎች ቁሳቁሶች ወድመዋል::>> በተያያዘ 20,000 ስደተኞችን እንደያዘ በተነገረለት ሽመልባ ለተሰኘ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ሰብአዊ ድጋፍ ማድረስ አልተቻለምብሏል:: የኢትዮጵያ መንግሥት በአካባቢው የህወሃት ታጣቂዎች የደፈጣ ውግያ በመጀመራቸው ለሁለቱየመጠለያ ጣቢያዎች አስፈላጊውን እርዳታ ለማድረስ መቸግሩን የሀገሪቱ የስደተኞች መርጃ ኤጄንሲአስታውቋል::