2021-03-29 07:06:07
ተስፋ ሊቆረጥለት አይገባም
ዲያብሎስ ዘመኑ እስኪጠናቀቅ ኃጢአት መስራትና እንዲሰሩ ማድረግ ወይም ክፋ ማሰብ እና ክፋቱንም የሰው ልጆች እንዲቀበሉት ማድረግ አያቆምም ፤
ከውድቀቱ ጀምሮ መልካም ነገር ሰርቶ አያቅም
ስለዚህ የሰው ልጆች የትኛውንም ያህል ኃጢአት ብንሰራ ከእርሱ እንደምንሻል ማወቅ አለብን ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር መንፈስ መልካም ስራ ሊያሰራን ይችላል ።
የሰው ልጅን ነፍስ ለክፋት እና ተስፋ ለማስቆረጥ ሚከራከራት ሰይጣን ነው አትድኝም ፣ አትፀድቂም ፣ አትለወጪም ወዘተ... በማለት ተስፋ ሳይኖረው ተስፋ ለማስቆረጥ ሚጥረው ነገረ ግን
ማስተዋል ያለብን ሰይጣን ነው ምህረት ስላሎደደ ያልዳነው ፣ ያልፀደቀው ፣ ያልተለወጠው ። ስለዚህ በዘመኑ ሁሉ የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ተጠግቶ መልካም ነገር ቢሰራ ፤ ለምሳሌ ስድስቱ ቃላተ ወንጌልን ቢፈፅም ፣ ቢፀልይ ወዘተ... መንፈሳዊ ትሩፋቶችን ቢሰራ ይድናል ዲያብሎስንም ያሸንፈዋል ። ምክንያቱም ሰይጣንና ሰራዊቱ ምህረት መጠየቅን እና መልካም ስራ መስራትን አሎደዱምና ። ስለዚህ ተስፋ ሊቆረጥለት አይገባም ምክንያቱም በምንም ቢሰላ በኃጢአት እሱ ይበልጠናል ። እኛ ግን ከእግዚአብሔር ይቅርታንና ምህረትን ለምነን ንስሐ ገብተን ቀኖናችንን ጨረሰን ፍትሐት ተደሮጎልን ስንቆርብ እና መንፈሳዊ ስራዎችን በቻልነው እና ባቅማችን ልክ በእግዚአብሔር እርዳታ ስንሰራ ፈጣሪያችን ይምረናል ይደሰትብናል ። ያኔ ሰይጣንንም እንበልጠዋለን ፤ ግን ከሰይጣን ጋር ለመፎካከር ሳይሆን ዋና ነጥቡ የሰው ልጆች የለበስነው ስጋ ድካም አለበትና ድንገት ባለማወቅ ፈጣሪያችንን ብናሳዝነው ተስፋ ለማስቆረጥ ቀድሞ ሚከሰን ሰይጣን ስለሆነ ተስፋ ሳንቆርጥ ከእግዚአብሔር ምህረት ተይቀን እንደምንድን እንድንነቃበት ነው ። ስለዚህ በሰው ልጅ መልካም ስራ እየቀናና እየተቃጠለ እየሰለቸው እየራቀን ይመጣል ።
@memher_eshetu
Comment @Channel_admin09
84 viewsEmu Ermias, 04:06