Get Mystery Box with random crypto!

​የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አጠቃላይ መረጃ የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሁለት ዞኖ | ኢትዮጵ

​የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አጠቃላይ መረጃ

የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሁለት ዞኖችንና ስምንት ወረዳዎችን አካቷል፡፡

የስፍራው አቀማመጥ
ክልሉ በኢትዩጵያ ምእራባዊ ጫፍ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፣ በምእራብ ደቡብና ሰሜን ሱዳንን ሲያዋስን፣ በደቡብና በምስራቅ ደግሞ የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትን ያዋስናል፣ እንዲሁም የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜንና ምስራቅ ያዋስኑታል፡፡
ርእሰ ከተማ
የክልሉ ርእሰ ከተማ ጋምቤላ ነው፡፡

የቆዳ ስፋት
ክልሉን በቅርቡ የተቀላቀለውን ወረዳ ሳይጨምር የክልሉ የቆዳ ስፋት 25‚274 ኪ.ሜ ይደርሳል፡፡

ስነ-ህዝብ
በ1987 በተደረገው የህዝብ ቆጠራ መስረት፣ የህዝብ ብዛቷ 182.862 ሲሆን ከነዚህ ውስጥም 92‚090 የሚሆነው ወንዶች ሲሆን 88‚960 ደግሞ ሴቶች ናቸው፡፡
153‚438 /84.9%/ የሚሆነው ህዝብ በክልሉ በገጠራማ ቦታዎች ውስጥ የኖራል፡፡
ዋና ዋናዎቹ የክልሉ ብሄረሰቦች ኑዌር፣ አኙዋክ፣ መዘንገር፣ አፓና እና ኮሞ ይባላሉ፡፡ በተጨማሪም የኦሮሞ፣ አማራ፣ ከምባታ፣ ከፉ፣ ትግሬ እና ሌሎችም ብሄረሰቦች በክልሉ ይኖራሉ፡፡
ከጠቅላላው የህዘብ ስብጥር 46 ከመቶ ኑዌር፣ 27 ከመቶ አኙዋክ፣ 8 ከመቶ አማራ 6 ከመቶ ኦሮሞ፣ 5.8 ከመቶ መዠንገር፣ 4.1 ከመቶ ከፋ ፣ 2 ከመቶ ሞካ ፣ 1.6 ከመቶ ትግሬ እና 5.5 ከመቶ የሚሆነው ደግሞ ከደቡብ ህዝቦች ናቸው፡፡

አማርኛ የክልሉ የስራ ቋንቋ ነው፡፡
የተለያዩ እምነት ተከታዬች የሚኖሩበት ክልል ነው፡፡ 44 ከመቶ የኘሮቴስታንት፣ 24.1 ከመቶ የኦርቶዶክስ፣ 10.3 ከመቶ የባህላዊ ሀይማኖት ፣ 5.1 ከመቶ የእስልምና፣ 3.2 ከመቶ የካቶሊክ እና 12.7 ከመቶ የሌሎች ሀይማኖት ተከታዮች ይኖሩበታል፡፡

ዋነኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች
አብዛኛው የክልሉ ህዝብ አርብቶ አደር ነው፡፡ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ሰሊጥና ሌሎች የቅባት ክህሎችን፣ ማንጐ፣ ሙዝና ወዘተ በማምረት ይተዳደራሉ፡፡
የመሬት አቀማመጥ እና የአየር ንብረት
ክልሉ በአብዛኛው ጠፍጣፋ የመሬት አቀማመጥ ሲኖረው፣ እርጥበት ያለው ሞቃት የአየር ንብረትን ይዟል፡፡
ለ17 አመት የተመዘገበው አመታዊ የአየር ንብረቱ 615.9 ሚ.ሜ ሲሆን፣ 21.12ocዝቅተኛ እና 35.9ocከፍተኛ የሙቀት መጠን በአማካኝ ተመዝግቦል፡፡

ወንዞችና ሀይቆች
ባሮ የተባለው፣ በኢትዮጵያ ሙስጥ ብቸኛው ለመጓጓዣ የሚያገለግለው ወንዝም በዚሁ ክልል ነው የሚገኘው፡፡ ወንዙ ክልሉን ከሱዳን ጋር ያገናኛል፡፡

ቱሪዝምና ቅርሶች
የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ በክልሉ የሚገኝ የቱሪስት መሰህብ ነው፡፡ በተጨማሪም እንደ ዝሆን፣ ጐሽ፣ ዝንጀሮና በቀቀን የመሳሰሉ የዱር እንሰሳት ይገኙበታል፡፡