Get Mystery Box with random crypto!

#Konso #Ale #Amaro 2023 ተማሪዎች የድጋሜ ፈተና ይወስዳሉ። በኮንሶ ዞን ፣ በአማሮ | Freshman course

#Konso #Ale #Amaro

2023 ተማሪዎች የድጋሜ ፈተና ይወስዳሉ።

በኮንሶ ዞን ፣ በአማሮ ልዩ ወረዳ እንዲሁም ኧሌ ልዩ ወረዳ በፀጥታ ችግር ውስጥ ሆነው የ2013 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈትነው ውጤት ያልመጣላቸው ተማሪዎች ከ2014 ተፈታኞች ጋር ድጋሚ ፈተና እንዲወስዱ ተወስኖላቸዋል።

ትላንትና የኮንሶ ዞን 773 ተማሪዎች ከ5 ትምህርት ቤቶች የድጋሜ ፈተና እንዲወስዱ መወሰኑን መግለፁን የሚመለከት መረጃ ልከንላችሁ ነበር።

ከኮንሶ ዞን ባለፈ በአማሮ ልዩ ወረዳ 7 ትምህርት ቤቶች 1171 ተማሪዎች በኧሌ ልዩ ወረዳ በ3 ትምህርት ቤቶች 79 ተማሪዎች የድጋሜ ፈተና እንዲወስዱ ተወስኖላቸዋል።

በአጠቃላይ በአንድ ዞን እና ሁለት ልዩ ወረዳዎች የድጋሜ ፈተናውን የሚወስዱት 2,023 ተማሪዎች ናቸው።

እነዚህ ተማሪዎች በአካባቢያቸው ላይ የፀጥታ ችግር በተደጋጋሚ እየተከሰተ ከፍተኛ በሆነ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ ሆነው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የተፈተኑ ሲሆን ነገር ግን ወደ ዩኒቨርሲቲ ሊያስገባቸው የሚችል ውጤት ሊያመጡ አልቻሉም።