አንቺ ባለሽበት ፣ሚባለውን እንጃ እኔ ባለሁበት ፣ ወሬ እንደጠብ መንጃ የታጠቀ ሞልቷል ፣ ቢደላም ቢከፋም ጆሮ አይሰማው የለም የሚበላ እንጂ ፣ የሚባል አይጠፋም ! #ይባላል ! ።። ለምሳሌ ያህል ትጥቃችን ባያልፍም ከዱላ ከድንጋይ ፣ ግፋ ቢል ከክላሽ ወዮለት ለጠላት ፣ ኋላ እንዳይበላሽ ኒውክለር ሲመካ አደቧን ትያዝ ግብፅ ፣ ትረፍ አሜሪካ አላርፍም ካሉ ግን ፣ ወየው ለሁለቱም ባለም ፊት ፈስ በፈስ እንዳናደርጋቸው በእጃችን ነው ያለው ፣ ደብተራም መተቱም ይባላል ፣፣፣፣ ለምሳሌ ያህል ሰማንያ ሺህ ዳቦ ፣ ሊያውም በአንድ ቀን ሊጋገር ነው ሲሉን ፣ በምን መብራት ብለን ፣ አናውቅም ጠይቀን እንዲሁ በማመን ፣ ሆዳችን ይሞላል በመሪ አንደበት ደም ያፀናው ሰንደቅ ፣ ጨርቅ ነው ይባላል። ።።። እኔ ባለሁበት ፣ በመኖሬያዬ ሀገር ከፀሐይዋ በታች ፣ የማይባል ነገር አንዳች አይገኝም ፣ ሁሉ አፉን ያክላል የሚለው ያጣ ሰው የተባለን ነገር ፣ "አይባልም "ይላል ።። የሆነው ሆነና ፣ ባለሁበት ሀገር የማይባል ነገር አጋጥሞኝ አያውቅም ለምሳሌ ያህል አባይ በአምስ አመት ተገድቦ ያልቃል በኢትዮጵያ ምድር ፣ ፀሀይ አትጠልቅም አስራ አንድ ፐርሰንት ሀገሪቱ አድጋለች ፣ በኑሮ ብንደቅም ስልጣን የህዝብ ነው ፣ ግን ለህዝቡ አንለቅም ይባላል ። ለምሳሌ ያህል ባይቆጥራቸው እንጂ፣ ዘንግቶ ምናልባት ጠቢቡ ሶሎሞን ከጠቢቡ በላይ ፣ አይበልጥም በእቁባት #ይባላል በላይ በቀለ ወያ ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 793 viewsAbela, edited 04:27