ኑ በተስፋ እንኑር! (ታደሰ ደምሴ) እንዲያ ...በደቦ እየጠጣን ከጠላቤት አለም በሀሳዊ ትምቢት ሰክረን ያለምነው ህልም እንዲያ በደመነፍስ... ከስጋ አምሮት እቶን ወድቀን እየጋየን ያልኖርነውን ህይወት... በረከሰ ምላስ ፅድቅ እየወለዠን የቆጠርነው ሱባይ ተሳልቆ ከከዳን ኑ! በተስፋ እንደር... ኑ! በተስፋ እንኑር... እንበል "መኸር ደርሷል ቀን ይወጣል" ዳግም ምን ሳይሰምር ቢቀር ተስፋ አይነፈግም!!! #ሼርርርር @Maryam21161 ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 2.7K viewsAbela, 11:58