"ላንቺ . . . ብለሽኛል - ያን ነኝ! ላንቺ መታመን ነው - አምላክ የሚያደርገኝ። - ያልሽውንም - ያን ነኝ! ላንቺ መሞቱ ነው - እኔን የሚያኖረኝ። ... አስቀድሞስ ቢሆን የፍጥረት ዘር እጁ ላንቺ መንገድ እንጅ - መች እግር አድርጎኝ ሢሠራኝ በደጁ። ላንቺ መንገድ ጥርጊያ ላንቺ አስቀድሞ ቃል - ትምርት ወንጌል መርጊያ! ላንቺ ንድፍ ዮሐንስ - ለሙሉ ስዕልሽ ለሚሆን ኢየሱስ! ለመጬመር ያህል... አሽዋው የአብርሐም የያዕቆብ ኮከብ ዘር ቃል እየቸገነ ግዛት እስኪጠበው - ኃይል እያገነነ የበዛው --- የፈላ --- የረባው ፈጣሪ ከፍጡር ካንቺ እስኪወለድ ነው። ዲበኩሉ ጌታ ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 2.3K views17:12