ቀድሼ :ላግባሽ.. 2.... የጸሎተ:ሐሙስ:የክርስቶስ:ራት በረከት:የቀመሽ:በፈለግሽው:ሰዓት ልሳንሽ:ወለላ:ፊደላትሽ;ስኳር እንደ:ዮሐንስ:አፈ:ወርቅ:አፈ;ማር:አፈ:ማር ! : በዻውሎስ:መፅሐፍ:እንደተነገረው የስጋሽን:መንፈስ;ስሜት:ሳያረክሰው በመንፈስ ቅዱስ :ኃይል:የከበረውን:ቤት በወጣትነትሽ:የጠበቅሽ:ክቡር:ሴት የዘመኑ :ልማድ:የዘመን:ፍካሬ ያላስገረሰሰው:የህግሽን :ፍሬ መዐዛው:ያራቀሽ:የክብር:ከልበኔ ምስጢሩ:የገባሽ:የወንጌሉ:ቅኔ በግዕዝ:በዕዝል:ስርአት:መልሼ እባክሽን:ላግባሽ:ራሴው:ቀድሼ!! ምዕመን:ይጠንቀቅ:ዘንድ:ከዝሙት:ፈተና አንድ:ሰው:ካንድ:ሰው:ወንጌል;ፈቅዷልና ።።ቃል:ለሰማይ :ብለሽ:እኔም:ቃል ;ለምድር የአብርሃምን:ህይወት:እባክሽ:እንጀምር! በጌታ:ተአምር:በስልጣኑ:ቀመር ፀንቻለሁና:ከእስጢፋኖስ:ማህበር ነጠላ:ሳትጥዪ:ቀለም:ሳትቀቢ አይንሽን:ሳይጋርድ:እኩይ:እንደረቢ ጸዋጋን:ሳይሰልቡን:ጠብቀው:አሳቻ ጥበብ:እንድስይሸሸን:የእግዚአሔር:ፍራቻ ላንቾም:ጸጋ:ጽናት:ለኔም:ህይወት:ብርታት እንዲወረብልን:ትዌድሶ:መርዓት...*... : በእዝል:በግእዝ:ስርአት:መልሼ እባክሽን:ላግባሽ:ራሴው:ቀድሼ!! Poet :Dawit tumey ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 3.6K viewsAbela, 16:23