ጓደኛ የጭንቀቴ ሸክም አላራምድ ብሎ፥ሲያስድኸኝ በዳዴ፤ የኑሮ ውጥረቷ ላይታች ጠፍሮ፥አለምድ ሲል ሆዴ፤ "ምን ሆንክ?" በለኝና ችግሬን አብርረው፥ተው አግዘኝ ጓዴ፤ ጭንቅህ ጭንቄ ይሁን፥መንገድህ መንገዴ! ከአንድ ሆድ ባናድር . . . ኖረን በአንድ መንደር፤ በአንድነት ገምደውን . . . እምነትና ፍቅር፤ ዛሬ እንደ ባይተዋር ችግሬን ታቅፌ ለምን ብቻ ልቅር? . ከየት ተደብቆ? . ላንተ መቼ ጠፍቶ ውስጤን እያነበብክ፥በፊት ገፄ መድረክ፤ ዓይኔን ካየኃቸው ከሊቅ እስከ ደቂቅ፥የለም የሚደበቅ፤ ክፍተትህን ልሙላ ከጎኔ ሁንና፥ሸፍን የኔን ስንጥቅ፤ አንተም በኔ ፈንድቅ፤ እኔም በአንተ ልድመቅ..! ላርም ስህተትህን . . . የአይምሮህን ፍዳ፤ ጥረገው ሰንኮፌን . . . ከህይወቴ ሜዳ፤ አይደለሁ የአዞ አልቃሽ . . . አይደለህ እንግዳ... ከጥንት ከበፊቱም የህይወት ቀኖናን፥ከአስተምሮት ጓዳ፤ ንዋይ አሸንፎት አሳልፎ ባይሰጥ፥ወዳጁን ባይከዳ፤ ከልቡ የመረጠው ጓደኛው ነበረ፥ለኢየሱስ ይሁዳ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 4.5K viewsAbela, 12:58