ጉልበት ቆጥቢያለሁ (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ልጅነቴ አክሮባት አልሰራ ልክ እንደታች አምናው ፥ ብረት አልጠመዝዝ ጠማማን አልገራ፥ ክንድ አልለካካ ፥ ከጎበዞች ጋራ እግሬ አጭር ተራምዶ፥ በረጅሙ አረፈ እግዜር እድሜ አይጨምር፥ አቅምን ካልሸረፈ : : ልቦናሽ ታውኳል? ‘የፈራው ደረሰ አቅሙ ተቀነሰ ይስለመለም ጀመር፥ እንደ ቁራጭ ሻማ፥ በነፋስ ክንፍ ፊት እንደተለኮሰ ‘ የሚል ፍርሀት ይዞሽ እንግድያውስ አይዞሽ! የሌለን ቢመስልም፥ ሀይልና ወኔ አለን፥ የምናስቀምጠው፥ ለክፉ ቀን ብለን :: ሲያምርሽ አፋፍሼሽ ፥ እስካልጋየ ድንበር ሲያምሽ ተሸክሜሽ ፥ እስካምቡላንሱ በር የምራመድበት ጉልበት ቆጥቢያለሁ፥ ከቁንጮ እስከ ሽበት ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @bewketuseyoum19 @bewketuseyoum19 9.0K viewsAbela, 10:50