የአዉሮጳ ሕብረትና ትግራይ የአዉሮጳ ሕብረት ባለስልጣናት ትግራይ ዉስጥ የተከሰተዉ ሰብአዊ ቀዉስና ባካባቢዉ ሊያስከትል የሚችለዉ ተፅዕኖ እንደሚያሳስባቸዉ አስታወቁ። የሕብረቱ የዉጪ ግንኙነት ኃላፊ፣የአስቸኳይ ርዳታ ኮሚሽነር እና የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር በጋራ ባወጡት መግለጫ የርዳታ ድርጅቶች ወደ ትግራይ ክልል በሰፊዉ መግባት እንዲችሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ይፈቅድ ዘንድ ጠይቀዋል። https://p.dw.com/p/3p82x?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot 3.7K viewsDW Amharic, 17:06