Get Mystery Box with random crypto!

በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የተደረገው ጦርነት በርካታ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ማስከተሉ ሲነገር ቆ | DW Amharic

በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የተደረገው ጦርነት በርካታ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ማስከተሉ ሲነገር ቆይቷል። ጦርነቱን ተከትሎ ከደረሰው የህይወት እና የአካል ጉዳት ባሻገር የዜጎች ከመኖርያ ቄዬአቸው መፈናቀላቸው እና በርካታ ማሕበራዊ ችግሮች መፈጠራቸውም እንዲሁ በመንግስትም ሆነ በሌሎች አለማቀፍ የመገናኛ ብዙኃን እና ተቋማት በኩል መረጃዎች ሲወጡ ቆይቷል። በትግራይ ክልል ከተፈጠረው ቀውስ ባሻገር በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚደርሱ ሰብአዊ እና ሌሎች ፖለቲካዊ አንድምታ ያላቸው አለመረጋጋቶችን በተመለከተ ከመንግስትም ሆነ ከሌሎች አካላት የሚወጡ መረጃዎች ሚዛናቸውን ያልጠበቁ ስለመሆኑ ሲነገር ይሰማል። በትግራይ ክልል የተከሰተውን ቀውስንም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚደርሱ ሰብአዊ ችግሮች በመንግስት ፣ በሌሎች የአለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና የረድኤት ድርጅቶች የሚወጡ መረጃዎች ምን ያህል ሚዛናቸውን የጠበቁ ናቸው? እርስ በእርሳቸው የተጣረሱ መረጃዎች እንዲወጡ ምክንያቱ ምን ይሆን የዜጎች ትክክለኛ መረጃን ከማግኘት መብት እና ከወገንተኝነት የጸዳ እና ትክክለኛ መረጃ ከማግኘት አንጻር ምን መደረግ አለበትስ ትላላችሁ? ሀሳባችሁን አካፍሉን።