🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

​​ የጠፋው ሬሳ #ክፍል ሀያ-ሁለት ፡ ...ብልጭ ድርግም በሚለው የሆስፒታሉ መብራት የሆነ ሰ | Emoji feelings🦋

​​ የጠፋው ሬሳ
#ክፍል ሀያ-ሁለት


...ብልጭ ድርግም በሚለው የሆስፒታሉ መብራት የሆነ ሰው ይታየኛል አሁን ፊቴን አኮሳትሬ ግንባሬን ጨምድጄ እልሄን ሰብስቤ ወደፊት መጠጋቴን ጀመርኩ የጓደኞቼን ደም ለመበቀል ከመፈለጌ የተነሳ ወደኔ እንኳን እስኪመጣ አልጠበኩትም ራሴ ተጠጋሁት የያዝኩትን ቢላ ዘቅዝቄ እጀታውን በማርያም ጣቴ ጋር አድርጌ ስለቱን ወደ ክርኔ አስደግፌ በለዘበ አረማመድ መጠጋቴ ቀጠልኩ ነገር ከኔ ተቃራኒ ጥግ ላይ ያለው ሰው አይንቀሳቀስም ለምን እንደሆነ ባላውቅም እኔ ግን በድፍረት እና በንዴት እየተጠጋሁት ነው...የሆስፒታሉ መብራት ብልጭ ድርግሙን ትቶ ቀጥ ብሎ በራ ጥግ የተመለከትኩት ነገር አይደለም ሊገለኝ ይልቁና በፍርሃት ተሸማቆ ራሱን አሳንሶ ተኮራምቶ ፊቱን ሸሽጎ ተቀምጧል..."እንደ ወንድ ተነስተህ ና እንደ ፈሪ አትሸፋፈን እንደ ገዳይ ፊት ለፊት ውጣ አትርመጥመጥ" አልኩት ንግግሬን በእርጋት ጀምሬ ንዴቴ ሲብስ እየጮውኩኝ ነገር ግን አሁንም ዝምታ ነበር መልሱ...ወደሗላ አድርጌ የነበረውን ስለት ወደ ፊት መልሼ ደረቱ ላይ ለመሰንቀር ወደ ተቀመጠበት ስፍራ ኮቴ ቢስ በሆነ እርምጃ ተጠጋሁት ነገር ግን ከሗላይ በሰከንድ ሽርፍራፊ እጅግ ፈጣን ሰው አለፈ...ከመቅፅበትም ፊቴን መልሼ የያዝኩን ስለታማ ቢላ ሰነዘርኩኝ ነገር ግን አንዳች ያጠቃሁት ፍጡር የለም ከአጠገቤ ያለው የሆስፒታሉ ክፍል አሁን እንደተከፈተ ያስታውቃል እንቅስቃሴውን እንኳን አላቆመም...በጥሞና ዙሪያ ገባዬን ቃኘሁኝ ግን ማንም አልነበረም ከቆምኩበት ሁለት ከፍል አለፍ ብሎ የሚገኘው ሶስተኛው ክፍል ሲከፈት ተሰማኝ ሆስፒታሉ ፀጥ ብሎ ስለነበር ሲከፈት ያለው የበር ድምፅ ይሰማል "ሲጢጥ" ሲል....አሁን መሃል ላይ ገብቻለሁ ከፊትለፊት የሆነ ሰው አለ ከሗላ ደግሞ ተኮራምቶ የተቀመጠው ፡...ዞር ብዬ ጀርባዬን ቃኘው ማንም ያ ሰው አሁንም ኩርምት እንዳለ ነው የመግደልም አቅም ያለው አልመሰለኝም ልክ እንደኔና ጓደኞቼ ጥቃት የደረሰበት ሊሆን እንደሚችል ገመትኩ ይሄን ሁላ ማሰላስለው ሲከፈት ድምፁ ወደተሰማኝ በር እያመራሁ በአይኖቼም መለስ ብዬ ጀርባዬን እየተመለከትኩ ነው አሁን ክፍሉጋ ልደርስ አንድ እርምጃ ያህል ቀርቶኛል የቀረኝንም እርምጃ እግሬን አንስቼ ልራመድ ስል መብራቱ ድርግም ብሎ ጠፋ ከመቅፅበትም አጠገቤ ያለው ግድግዳ ላይ ተደግፌ ቁልቁል ወርጄ ድምፄን አጥፍቼ ፀጥ አልኩኝ በጨለማው መሀል የትልቅ ከስክስ ጫማ ድምፅ ተሰማኝ ሰፋ ያለ የእግር አጣጣል እንዳለው ከምሰማው የእግር ኮቴ ተረዳሁ ውስስጤ ፍርሃት የሚባል የለም በቀል እንጂ ነገር ግን ጨለማወው ነገሮችን በብዙ እያከበደብኝ ነው "ቢሆንም ግን ገድዬው ወይ ገሎኝ ከዚ አረመኔ ነፍሰ በላ ጋር እለያያለሁ" አልኩኝ ለራሴ እርምጃው እየቀረበኝ ነው የያዝኩትን ስለት በተጠንቀቅ አዘጋጅቼ እየጠበኩ ነው...በድንገት መብራቱ ፏ ብሎ በራ ከተቀመጥኩበት ተስፈንጥሬ ተነስቼ የእግር ዱካው ይሰማኝ ወደነበረው ስፍራ የያዝኩትን ስለታም ቢላ ሰነዘርኩኝ ነገር ግን ማንም አልነበረም ወዲያውኑ ጎላና ጎርነን ባለ ድምፅ ልብን የሚያርድ ሳቅ ተሰማ ባለሁበት ተንበረከኩ እንደሚዲህ ህፃን ቀዳዴ እየሄድኩ ግራና ቀኜን ተመለከትኩ ነገር ግን ምንም የለም ነበር ሳቁ ሳቅ ብቻ አይደለም አንዳች ሃይል አለው ቁጣዬን ነጠቀኝ እልሄን በፍርሃት ለወጠው በቀሌን የሽሽት አደረገው በጣም ተደነኩኝ አብዝቶም ገረመኝ ካልመጣ ስል የነበርኩት ቤት ልውጣ ብዬ ተጨነኩኝ ጣቶቼ ቢላውን መጨበጥ እስኪያቅታቸው ተብረከረኩ በዛ የውድቅት ምሽት ከየት መጡ የማይባሉ ቁራዎች ሆስፒታሉ ውስጥ ተመሙ ራሳቸውን ከግድግዳ ጋር እያጋጩ ኮሪደሩን በደም አጨቀዩት አብዝተውም ይጮሁ ነበር መሃል ላይ ሆኜ በግንባሬ ከወለሉ ተዋድጄ ሞቴን መጠበቅ ጀመርኩኝ አቀርቅሬ ባለሁበት ጊዜ አንገቴ ላይ ያለው የብር ሃብል ወለሉ ላይ ተመለከትኩት ግንባሬንም ቀና አድርጌ የዓለም ሁሉ ቤዛ የሆነው አንድ አምላክ የተሰቀለበት መስቀል ነበር መስቀሉ ላይም የኔ እና የዓለሙ አዳኝ እንዳላቀረቅር አቀርቅሮ አየሁት ህመሜን ታሞልኝ ተቸንክሮ አየሁት....እሱን ባየው ጊዜ ንዴቴ እና እልሄ መታደስ ጀመረ ስልቱን ጨብጬ በሁለት እግሬ ቆምኩኝ ነገር ግን ሆስፒታሉ በደም ጨቅይቶ የነበረው በቁራ ድምፅ የታወከው ስነሳ ግን ሰላም ነበር...መጀመሪያ ጥግ ላይ ካየሁት ሰው በቀር በድጋሜ ማንም አልነበረም ወደዛም ሰው ቀጥ ብዬ ተጠጋሁ ስደርስም "እባክህ አትግደለኝ እባክህ" እያለች ሳግ እየተናነቃት የምትማፀን ሴት ነበረች "አይዞሽ አልጎዳሽም ተነሺ" ስላት "ሜርሲዬ" ብላ አቀፈችኝ የመየውን ማመን አልቻልኩም ሞቱ ካልኳቸው ጓደኞቼ መሃል ቄድስቴ ነች "ቅድስቴ አንቺ ነሽ እንዴ ተጎዳሽ የሆንሽው ነገር አለ?" ብዬ ጠየኳት ሰውነቷን እየደባበስኩ "ምንም አልሆንኩም ባባን ወስዶታል ባርሳ ደሞ የት እንዳለች አላውቅም" አለችኝ "አታልቅሺ እናገኛቸዋለን" ብዬ አባበልኳትና እጇን ይዤ ወደ መውጫው ሳመራ "ሜርሲዬ ይሄ ለመገለን የሚፈልገው ሰው ትዝ ካለሽ ከወር በፊት ጠፋ የተባለ ሬሳ ነበር ሰዎችም እንደሚሉትም ሞቶ የተነሳ የመናፍስት እጅ ያለበት...እያለች እየነገረችኝ ሳለ ዞር ብዬ የምትለው ገርሞኝ እንግዳ ሆኖብኝም ልሰማ ስቆም ሰውዬው ከየት መጣ ሳይባል የእግሩ ዱካ ሳይሰማ አንዳችም ነገር ሳይታወቀን በንፋስ ፍጥነት ከቅድስታ ጀርባ ቆሟል..............

..........ይቀጥላል...........

ቀጣዩን#ክፍል ሀያ ሶስት እንዲቀጥል
ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
አሰተያየት ካላችሁ አድርሱን


Join&share

ማንበብ ባህላችን ይሁን