Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵ የኢትዮጵያ አጠቃላይ መረጃ •መልክዓምድር ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ከ3-14 ዲግሪ | ኢትዮጵ

ኢትዮጵ
የኢትዮጵያ አጠቃላይ መረጃ

•መልክዓምድር
ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ከ3-14 ዲግሪ ሰሜን እና ከ33-48 ዲግሪ ምሥራቅ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. ነው።
በሰሜን ከኤርትራ፣ በምዕራብ ከሱዳን፣ በደቡብ ከኬኒያ፣ እንዲሁም በምሥራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች።

የኢትዮጵያ አብዛኛው ግዛት በተራሮችና በሀይቆች የተሞላ ሲሆን፣ ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምሥራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመጋደም ለሁለት ይከፍላቸዋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይኅን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪቷ የተለያዩ የአየር ንብረት፣ የአፈር፣ የዕፅዋት እና የሕዝብ አሰፋፈር ገጽታዎች እንዲኖራት አስችሏታል።
(ምስል 1•የኢትዮጵያ ካርታ 2•የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ)

በከፍታና በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዐይነት የአየር-ንብረት ክልሎች ይገኛሉ።
እነሱም:-
➊ደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግረ ሴ.ግ የማይበልጥ፤
➋ወይናደጋ - ከፍታቸው ከባሕር ጠለል ከ1500 እስከ 2400 ሜትር፣ ሙቀታቸውም ከ16 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 30 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስና፣
➌ቆላ - ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ30 ዲግረ ሴ.ግ እስከ 50 ዲግረ ሴ.ግ የሚደርስ አከባቢዎች ናቸው።

ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።
•የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ነው

•አጠቃላይ ታሪክ

ከጥንት ጀምሮ ከነበሩ አገሮች የምትመደብና በአፍሪካ ከሚገኙ አገሮች ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ ያስቆጠረች አገር ነች፡፡ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን /ድንቅነሽን/ አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡

በአራተኛው ክፍለ ዘመን ከግብጽና ሶሪያ ሚሲዮኖች መጥተው ክርስትናን ለኢትዮጵያ አስተዋውቀው ነበር፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትና ርቃ ቆይታለች፡፡ ከዛም በ1500 ዎቹ ፖርቱጋሎች በህንድ ውቅያኖስ ላይ የነበራቸውን ይዞታ ለማጠናከርና ኢትዮጵያ ውስጥ የሮማ ካቶሊክን ለማስፋፋት ሲሉ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት መልሰው ጀምረው ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት አንድ ክ/ዘመን ያህል የፈጀ የሀይማኖት ግጭት በ1630ዎቹ ተነስቶ ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያንን በሙሉ ከኢትዮጵያ ተባረው ሲወጡ ተፈጽሟል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡

ከ1700ዎቹ ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም "የመሳፍንት ዘመነ መንግስት" የተለያዩ የኢትዮጵያን ክፍል ይገዙ በነበሩ ገዢዎች መሀል በነበረው ፉክክር የተነሳ በመጣው ብጥብጥ ሲታወቅ በ1869 ግን አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶችን አንድ ላይ በማምጣት ዋነኛ አሰባሳቢ ሀይል ሆነዋል፡፡ ተከታያቸው አፄ ዮሀንስም አፄ ቴዎድሮስ የጀመሩትን ቀጥለው ኢትዮጵያን ለመውረር ሙከራ ያደረጉትን ደርቡሾችና ሱዳኖችን ረተው መልሰዋል፡፡

ከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን ገዝተዋል፡፡ በዛ ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን አሸንፋ በአፍሪካ የቀኝ ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች፡፡

በ1908 የክርስትና ሀይማኖት ሹማምንት ልጅ እያሱን ለእስላሙ ህብረተሰብ በመቆርቆራቸው ምክንያት ከስልጣን አውርደው የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱን ስልጣን ላይ አውጥተዋቸዋል፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበረውም ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡

እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ስማቸውን ወደ ሀይለስላሴ በመቀየር ስልጣን ላይ ወጡ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ ይህን ጊዜም አፄ ሀይለስላሴ ለሊግ ኦፍ ኔሽንስ ይግባኝ ብለው ሰሚ ስላጡ ወደ እንግሊዝ ተሰደው ለሚቀጥሉት አምስት አመታት የኢትዮጵያ አርበኞች ከብሪታንያ ጋር በመተባበር ጣልያንን እስኪያሸንፉ ድረስ ወደ ስልጣናቸው አልተመለሱም ነበር፡፡

አፄ ሀይለ ስላሴ እስከ 1966 ድረስ ስልጣን ላይ ከቆዩ በኋላ በምትካቸው የጊዜአዊ ወታደራዊ ምክር ቤት /ደርግ - ኮሚቴ የሚል ትርጉም ሲኖረው/ ስልጣን ይዘው በስም ሶሻሊስት የሆነ በአቋም ግን ወታደራዊ አመራር ያለው መንግስት ተመሰረተ። ከዚህ ክስተት በኋላ ሻለቃ መንግስቱ ሀይለ ማሪያም እንደ ኘሬዝዳንትና እንደ ደርግ ሊቀ መንበር ስልጣን ያዙ፡፡

በ1980ዎቹ መጀመሪያ በኢትዮጵያ በተለይ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በሚገኙት ትግራይና ኤርትራ መንግስታዊ ግልበጣ ተካሄደ፡፡ በ1981ዓ.ም የትግራይ ህዝቦች ነፃ አውጪ ግንባር /ትህነግ/ ከብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ብአዴን/ እና ከኦሮሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/ ጋር አንድ ላይ በመሆን የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ን መሰረቱ በግንቦት 1983 ላይም የኢህአዲግ ሀይሎች ወደ አዲስ አበባ በመግባት ኮሎኔል መንግስቱ ወደ ዙንባቢዌ እንዲሰደድ ሆኗል፡፡
በ1983 ከኢህአዲግ እና ሌሎች የአገሪቷ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተውጣጡ 87 የተወካዮች ምክር ቤትና በሽግግር ህገ መንግስት የኢትዮጵያ ሽግግር መንግስት ተቋቋመ፡፡
በዛው አመት በኢሳያስ አፈወርቂ መሪነት የኤርትራ ህዝቦች ነፃ አውጭ ግንባር /ኤህነግ/ ከ30 አመታት ትግል በኋላ ኤርትራን ተቆጣጥሮ ጊዜአዊ መንግስት መሰረተ፡፡ እስከ ግንቦት 1985 ዓ.ም ድረስም ኤርትራዊያኖች በተባበሩት መንግስታት ክትትል የጠየቁት የመገንጠል መብታቸውን እስኪያገኙ ድረስ የጊዜአዊው መንግስትም ስልጣን ላይ ቆየ፡፡
በኢትዮጵያም ኘሬዘዳንት መለስ ዜናዊና የሽግግር መንግስቱ አባላት በሰኔ በ1986 ዓ.ም 548 አባላት ባሉት ለህገ መንግስታዊ ምክር ቤቶች ምርጫ ተካሄደ፡፡ በ1987ዓ.ም መጀመሪያ ላይ የተመረጡት የምክር ቤቱ አባላት የኢፌዲሪን ህገ መንግስት ተቀበሉ፡፡ የፖርላማ ምርጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው በ1987 ዓ.ም ሲሆን በዛው አመት ነሀሴ ወር ላይ መንግስት ተቋቋመ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊም ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመረጡ

☞ይቀጥላል☜