Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵ •የኢትዮጵያ አጠቃላይ መረጃ ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ ነሃሴ 14፣ 2004 ዓም ከዚህ | ኢትዮጵ

ኢትዮጵ
•የኢትዮጵያ አጠቃላይ መረጃ

ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ ነሃሴ 14፣ 2004 ዓም ከዚህ አለምበሞት ሲለዩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት ኃይለማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆነው ተሾሙ።

•የመንግስት አወቃቀር

ኢትዮጵያ የፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት አወቃቀር ሲኖራት በ10 የብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት እንዲሁም በሁለት የከተማ መስተዳድሮች የተዋቀረች ነች፡፡ አወቃቀራቸውም በሕገ መንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር ፣ ቋንቋ ፣ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም የሚከተሉት ናቸው።

1. የትግራይ ክልል
2. የአፋር ክልል
3. የአማራ ክልል
4. የኦሮሚያ ክልል
5. የሶማሌ ክልል
6. የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
7. የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል
8. የጋምቤላ ክልል
9. የሀረሪ ክልል
10. የሲዳማ ክልል
11. በተጨማሪም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳደሮች ይገኙበታል።

እነዚህ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት አንዲሁም ሁለቱ የከተማ መስተዳደሮች በ800 ወረዳዎቸና ወደ 15000 በሚጠጉ ቀበሌዎች(5000 የከተማና 10000 የገጠር) የተከፋፈሉ ናቸው።

•ህዝብ
በ1999 ዓ.ም በተደረገው የህዝብና ቤት ቆጠራ እና ትንበያ መሰረትም በአሁኑ ጊዜወደ 90 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ አላት፡፡ ከዚህም ውስጥ ወደ 84 ከመቶ የሚጠጋው በገጠሪቱ የኢትዮጵያ ክፍል ሲኖር የተቀረው በከተማና ከፊል ከተማ በሆኑ ቦታዎች ይኖራል፡፡

ኢትዮጵያ ከ80 በላይ የሚሆኑ ብሄር ብሄረሰቦች የሚገኙባት ሀገር ነች። የኦሮሞ፣ የአማራ፣ እና የትግራይ እንዲሁም የሶማሌ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የአገሪቱዋ ሕዝብ ቁጥር ክ3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ።
በሃይማኖት በኩልም ክርስትናና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። እስልምና ከ 25-30% ፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታዮች ከ 60-65% ፡ ፐሮቴስታንት ደግሞ 10% የሚሆነውን ድርሻ ይሸፍናል።
የወንድ አማካኝ እድሜ 53.42 ዓመት ሲሆን የሴት ደግሞ 55.42 ዓመት ነው።
የዕድሜ ስብጥር (በመቶኛ)
0-14 አመት - 42.8%
15-19 አመት - 10.5%
20-49 አመት - 37.4%
50-59 አመት - 4.9%
60ና ከዛ በላይ: 4.4%

•ቋንቋዎች

በኢትዮጵያ ውስጥ ከ80 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ80 በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገርባት ሀገር ናት፡፡
በአሁኑ ወቅት በእብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የብሄራዊ ቋንቋ ነው።
በኢትዮጵያ የሚነገሩት ቋንቋዎች ወደ አራት ዋና ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። እነዚሁም:-

#ኩሻዊ: ወደ 19 ቋንቋዎችን የያዘ
#የአባይ-ሰሃራዊ: ወደ 20 ቋንቋዎችን የያዘ
#ኦሞአዊ: ወደ 23 ቋንቋዎችን የያዘና
#ሴማዊ: ወደ 12 ቋንቋዎችን የያዙ ናቸው።

ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ ኦሮምኛ፣ ሶማልኛ፣ አፋርኛ፣ ሲዳምኛ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ፣ ኩናማኛ፣ ጉሙዝኛ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛ፣ ጋሞኛ፣ ከፋኛ፣ ሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ጉራጊኛ፣ ስልጢኛ፣ ሀደሪኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋንቋዎች ይመደባሉ።
የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ብቸኛዋ ባለ ጥንት ፊደል ሀገር ያደርጋታል። እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለእለት ተእለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው።

•ኢኮኖሚ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዋነኛነት በግብርና ዘርፍ የተያዘ ነው ከዚህም ከሀገሪቱ ጠቅላላ የውስጥ ምርት 45 ከመቶውን ይሸፍናል፣ 10 ከመቶ የሚሆነው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ሲሆን፣ 13.3 ከመቶው ደግሞ የማምረቻው ዘርፍ ይይዛል፡፡
የወጪ ንግድም የሚከናወን ሲሆን ከዚህም ውስጥ እስከ 60 ከመቶ የሚደርሰው የቡና መላክ ወጪ ንግድ ነው፡፡

•ግብርና

እርሻ የአገሪቱ የጀርባ አጥንት ሲሆን አገሪቱ ከዚሁ የኢኮኖሚ ዘርፍ ቡና፣ የቅባት እህሎች፣ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ስኳር እና የከብት መኖ ወደ ውጭ ትልካለች፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የከብት ሀብት ልማት በመኖሩ ከዚህ ዘርፍ የቁም ከብት፣ ቆዳና ሌጦ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ታገኛለች፡፡
ኢትዮጵያ ካሏት አጠቃላይ ዘርፎች ውስጥ የግብርና ዘርፍ ቀዳሚውን ሲይዝ በ2006/07 ዓ.ም በተገኘ አመታዊ ስሌት መሰረት ግብርና 45.9 ከመቶ የሚሆነውን የሀገሪቱ የምርት ውጤት ይሸፍናል፡፡ ወደ 45 ከመቶ የሚሆነው የሀገሪቱ መሬት ለግብርና ስራ ምቹ ነው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ወደ 10‚556 ሄክታር መሬት ብቻ ለእርሻ አገልግሎት የዋለ ነው፡፡

•የአምራች ዘርፍ

በ2006/07 ዓ.ም 13.3 ከመቶ የሚሆነውን የሀገሪቱን ጠቅላላ ምርት ያስመዘገበው ይህ ዘርፍ ነው፡፡ ከዚህም ዘርፍ የምግብ፣ የለስላሳ መጠጦች፣ የጨርቃ ጨርቅና የቆዳና ሌጦ ውጤቶች ይገኙበታል፡፡
ዘርፉ በዋነኛነት ከግብርና የሚገኙ ምርቶችን ለማቀነባበር እና ለማምረት ይንቀሳቀሳል፡፡ በዚህም ለሀገር ውስጥ ገበያ የሚውሉ የሸማቾች እቃዎችን ያቀርባል፡፡ ወደ ውጭ ከሚላኩ ምርቶችም ጨርቃ ጨርቅ፣ የታሸገና የቀዘቀዘ ስጋ፣ በከፊል የተጨረሱ ቆዳና ሌጦ፣ ስኳርና ሞላሰስ፣ የእግር አልባሳት፣ ትንባሆ፣ ለስላሳ መጠጦች፣ ዘይት፣ ሰም ፣ ሌዘርና የሌዘር ውጤቶችን ያቀርባል፡፡

•አገልግሎት ሰጪ ዘርፍ
የአገልግሎት ሰጪ ዘርፍ 40.5 ከመቶ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ምርት ይሸፍናል፡፡ ይህ ዘርፍ በአሁኑ ወቅት ቀስ በቀስ በማደግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በ1996/97 ዓ.ም ከነበረበት 36 ከመቶ በ2006/07 40.8 ከመቶ ሊደርስ ችሏል፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በተፈጠረው የትምህርት፣ የሪል-እስቴት፣ የኪራይ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች፣ በጅምላና ችርቻሮ ንግድ፣ እንዲሁም የሆቴልና ሬስቶራንት ንኡስ-ዘርፎች እድገት ምክንያት ነው፡፡

•የመገበያያ ገንዘብ:

የኢትዮጵያ የገንዘብ መለኪያ ብር ነው
1 ብር ከ100 ሳንቲሞች ጋር እኩል ነው
የብር ኖቶች
ባለ 1 ብር ኖት
ባለ 5 ብር ኖት
ባለ 10 ብር ኖት
ባለ 50 ብር ኖት
ባለ 100 ብር ኖት
የመዳብ ሳንቲሞች፡ 1፣5፣10፣25፣ እና 50 ሳንቲሞች
የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት በአየር መንገዶች እና ፈቃድ ባለቸው ሆቴሎች ይገኛል፡፡

ምንጭ
የኢትዮጵያ መንግስት ፖርታል
ማእከላዊ ስታትስቲክስ እጀንሲ
የኢትዮጵያ ብሄራው ባንክ ድረ-ገፅ