2023-03-27 08:11:14
" ትኩረት ሰጥተን ለመጫወት ተዘጋጅተናል "
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በዛሬው ዕለት ከ ጊኒ ጋር ከሚያደርጉት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ አራተኛ ጨዋታ በፊት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ካነሷቸው ነጥቦች መካከል :-
- ያለፈውን ጨዋታ ቶሎ ረስተን ስለቀጣዩ ጨዋታ በማሰብ ትኩረት ሰጥተን ቀጣዩን ጨዋታ ለመጫወት ዝግጅታችንን ጨርሰናል።
- ሚልዮን ሰለሞን በጉዳት ምክንያት ከጨዋታው ውጪ ነው ሌሎች ሁሉም ተጨዋቾቻችን ለጨዋታው ዝግጁ ናቸው።
- በባለፈው ጨዋታ ተጋጣሚያችን ካሳደረብን ጫና እና ብልጫ በላይ እኛ ጨዋታውን ለመቆጣጠር የሄድንበት መንገድ ልክ አልነበረም።
- በጨዋታ ውስጥ ማሸነፍ ፣ መሸነፍ እና አቻ ያለ ነው በጨዋታው የታየው እንቅስቃሴ እኛ በፈለግነው መንገድ አለመሄዱ ተጨዋቾቹ ካላቸው ጉጉት እና ፍላጎት የተነሳ ነው።
- ጨዋታውን የተሸነፍነው ያን ያህል ከባድ ሆኖ አይደለም ፣ ለራሳችን የሰጠነው ግምት እና ከ ጨዋታው እንፈልገው የነበረውን ውጤት በጉጉት በመጠበቃችን ነው።
- በጨዋታው ያደረግነው የአዕምሮ ጨዋታን ሳይሆን የጉልበት ጨዋታን መሰረት አድርገን ነበር ይህ ደግሞ ለእነሱ ተመችቷቸዋል።
- እነሱ የነጥብ ብልጫ ስላላቸው ወደ ሜዳ ይዘው የሚገቡት ነገር ሊኖር ይችላል እኛም ደግሞ የምንፈልገውን ነጥብ ለማግኘት የራሳችንን ዝግጅት አድርገናል።"ሲሉ ተደምጠዋል።
ምንጭ - የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን
@yenesport
367 viewsdavo2061, 05:11