Get Mystery Box with random crypto!

ኢዜማ በአዲስ አበባ ባለቤትነት ጥያቄ ላይ “የማመቻመች አቋም” እንደሌለው አስታወቀ የኢትዮጵያ ዜ | @እንደኔ እይታ.....

ኢዜማ በአዲስ አበባ ባለቤትነት ጥያቄ ላይ “የማመቻመች አቋም” እንደሌለው አስታወቀ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጥያቄ ላይ “ምንም አይነት ብዥታ” እንደሌለው እና በጉዳዩ ላይም “የማመቻመች አቋም” እንደማይከተል አስታወቀ።

ፓርቲው ይህን አቋሙን የገለጸው፤ ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 28 በአዲስ አበባው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል በነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ ነው።

የፓርቲውን መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ዕጩዎች በተገኙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስ አበባ ከተማን፣ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ እና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ፓርቲው የሚያራምዳቸውን አቋሞች እና አስተሳሰቦች የተመለከቱ ጥያቄዎች ከታዳሚዎች ተነስተዋል።

ሶስት መቶ የሚጠጉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተገኙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የከተማይቱ የባለቤትነት እና የልዩ ጥቅምን የተመለከቱ ጉዳዮች እና ራስን በራስ ማስተዳደርን የተመለከቱ ጥያቄዎች ለፓርቲው ዕጩዎች ቀርበዋል።

ሌሎች ክልሎች በአዲስ አበባ ላይ ያላቸውን ልዩ ጥቅም በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄ፤ የኢዜማ መሪ በሰጡት ምላሽ “ለአንድ ብሄር የሚሰጥ ልዩ ጥቅም አይኖርም” ሲሉ የፓርቲያቸውን አቋም አስታውቀዋል።

ከአዲስ አበባ መስፋፋት ጋር በተያያዘ ለተነሳው ጥያቄ ደግሞ “አዲስ አበባ መስፋት እስካለባት መስፋት ትችላለች” ብለዋል።

ነገር ግን ይህ የከተማዋ መስፋፋት በዙሪያዋ ያሉ ነዋሪዎችን በሚጠቅም እና በማይጎዳ መልኩ መሆን እንዳለበትም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/3470/