🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ቅኔ ያለው ትውልድ

Logo of telegram channel keney_serezoch — ቅኔ ያለው ትውልድ
Logo of telegram channel keney_serezoch — ቅኔ ያለው ትውልድ
Channel address: @keney_serezoch
Categories: Literature
Language: English
Subscribers: 1.33K
Description from channel

ለነፋሳቹ ነፋስ የሚሆኑ ነገሮችን ዝሩለት . . !
ቤቴን ቤቶ ስላረጉ አመሰግናለው!
. .

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 8

2021-06-01 06:31:12
………………

በቁመና ለማደግ ፣ወደብርሃን ለመጠጋት
በተፈለገ ጊዜ ፣ ስርን ወደ መሬት መላክ
ያስፈልጋል ፣ ወደ ድቅድቅ ጨለማው፣
ወደ ጥልቁ - ወደ መጥፎው።


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
106 views03:31
Open / Comment
2021-05-31 12:46:51 …………………

መፅሃፉ The Count of Monte Cristo ይሰኛል።

ፈረንሳይ ውስጥ በነበረው የፓለቲካ ሽግግር ሳቢያ ሁነቱ ሰለባ ስላደረገው ወጣት መርከበኛ ይተርካል።

ወቅቱ ናፖሊዮ እና ሊዊ 16 ኛ ያልረገበ ውጊያ የሚያካሂዱበትና መንበር ለመለዋወጥ የተፋለሙበት ጊዜ ነበር።

ይህን ደራሲው ለመፅሃፉ እንደ መቼት የተጠቀመው ሲሆን እልፍ ገፀባህሪያትን በመመስረት ታሪኩን ውብ አርጓ ይጓዛል።

አብዛኞች ድርሰቶች ታሪክ የሚነግሩበት የሴራ አወቃቀር ቀጣዮቹን ዋና ክፍሎች ይዞ የሚከወን ሲሆን

የታሪክና ገፀባህሪ ትውውቅ (exposition)
ግጭት (conflict)
ጡዘት/ልቀት (climax) ከደረሰ በኋላ
የሁነት መርገብ (Falling Action)
የትልም ማሳረጊያ (resolution ) ላይ በመድረስ ይጠናቅቃሉ።

ይህን መፅሃፍ ልዩ የሚያደርገው የትልም / ሴራ (plot) አመሰራረቱ እንደማንኛው መፅሃፍት ከላይ የተጠቀሱትን ዋና ክፍሎች አንድ ጊዜ ሳይሆን በየምዕራፉ በተደጋጋሚ የተለያዩ ገፀባህሪያትን በመምዘዝ አስተዋውቆ ግጭት ፈጥሮ ልቀት ላይ አድርሶ ግጭቱን በማርገብ መልሶ ወደ ነበረበት ዋና ታሪክ ወይም ወደ ዋናው ገፀ ባህሪ የብቀላ ጉዞ መግባቱ ላይ ነው። ይህ ደግሞ ሰውየው አንዲት ትንሽ ሴራ ብልጭ ብላላቸው ሳትጠፋባቸው እንደሚፅፉ ምስኪን ፀሃፍት የሴራ አወቃቀር ድሃ እንዳልነበር ያሳያል። የትኛውም ገፀባህሪ ታሪክ ያለምክኒያት ጥራዝ ለማደለብ እንዳልተካተተ ሲገባህ ዱማስ የትልም ቁንጮ መሆኑን ትረዳለህ

ይህን አይነት የሴራ አመሰራረት ለመካን አይነተኛው መንገድ በንባብ እውቀትን ማስፋት ነው።

ተሾመ ዳምጤ ወደ አማርኛ ግሩም አድርጎ መልሶታል። በሆሊውድ መንደር ፊልምም ተሰርቶለታል። ባታዩት እመክራለሁ። "የአለማችን አስቀያሚው የመፅሃፍ ታሪክን ወደ ፊልም ቅየራ" ቢባል ሲያንሰው ነው። በበርካታ የታሪክ ፍሰት ስህተቶች የተሞላ በመሆኑ ፊልሙን ብቻ በማየት መፅሃፉን ካነበቡ እኩል ለውይይት እንዳትጋበዙ . . . .

ያላነበባቹት እድታነቡት የሰኞ ግብዣ ነው

╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
140 views09:46
Open / Comment
2021-05-31 12:45:37
126 views09:45
Open / Comment
2021-05-31 06:18:52
ሽንፈትና ድል
<_>

የአንድ እናት ልጆች
ከደቂቅ ልዩነት ፈሰው የተመሙ
አምጠው ቦርቡረው
ክፍተቱን አብሰው ከሜዳ ገጠሙ።

ተቋስለው ተዳምተው
ብርቱ የጣለ 'ለት
ባንዱ ሙሉ ድል ውስጥ
አለ ግማሽ ሽንፈት።
__{ሱ አ}


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
43 views03:18
Open / Comment
2021-05-30 10:42:01
ቀን / 22 9 2013 እሁድ

……… ዛሬ ምናወድሳቸው ጀግና



እናት ወ/ሮ አበበች ጎበና

በ1938 ሸዋ ውስጥ ሰላሌ አውራጃ ልዩ ስሙ ሸበል የሚባል የተወለዱት ባለ መልካም ልብ ሴት፤ አባታቸው በጣሊያኖች ስለተገደሉባቸው አያታቸው ጋር አደጉ፤ እንደ አገሩ ወግ ተድረው ኑሮን ቢሞክሩትም ስላልሆነላቸው ሁሉንም ነገር ትተው አዲስ አባባ መጥተው መኖር ጀመሩ፡፡
እንደ አጋጣሚ ከዛሬ 30 ዓመታት በፊት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ለሃይማኖታዊ ጉዞ ያቀናሉ። እናም ያኔ ወቅቱ በሀገሪቱ የረሃብ አደጋ ያጠላበት ጊዜ ነበርና አንዲት ሕፃን የእናቷ አስክሬን እቅፍ ስር ሆና ጡት ለመጥባት ትሞክራለች። ይህ ትዕይንት እጅግ ከፍተኛ ሐዘን ውስጥ ይከታቸዋል። ሕፃኗን ከሌላ አንዲት ሕፃን ጋር ይዘውም ለማሳደግ ይወስዳሉ። እናም ወዲያው 21 ሕፃናትን ለመርዳት ያሰባስባሉ። ሆኖም ባለቤታቸው እና የሥራ አለቃቸው ከሕፃናቱ ወይ ከእኔ አለያም ከሥራዎ የሚል ከባድ አጣብቂን ውስጥ ይከቷቸዋል። ሆኖም እሳቸው ሕጻናቱን ይመርጣሉ።

እንደዚህ የተጀመረው መልካምነት ቀጥሎ በአሁኑ ወቅት የክብር ዶክተር አበበች ጎበና በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች ከ12 ሺህ በላይ ሕፃናትን ይረዳሉ። በእሳቸው የእርዳታ ድርጅት ሥር ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተጠቃሚ መሆናቸው ይነገራል። በሰብአዊ እርዳታ ለጋሽ ድርጅታቸው 265 ቋሚ እንዲሁም 400 ሌሎች ሠራተኞችን ቀጥረው ያሰራሉ፡፡


የመልካምነት ውሃ ልኩ


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
119 views07:42
Open / Comment
2021-05-30 07:06:08
ቀን / 22 9 2013 እሁድ

የሳምንቱ የቻናሉ ምስል ……………


•••••• ይናገራል ሚስጥር••••••


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
31 views04:06
Open / Comment
2021-05-29 11:40:41
___

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር ነው ። ብዙዎቻችን በልቦለድ ስራዎቹ እናደንቀዋለን። በብዕር ስሙ ሠርቅ ዳ.፣ በትክክለኛ መጠሪያው ዳንኤል ጎበና ይባላል ። በ1958 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተወለደ። የአንደኛ ና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በቅዱስ ዮሴፍ ና በካቴድራል ትምህርት ቤቶች ተከታትሏል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሳይኮሎጂ የመጀመሪያውን ዲግሪ አግኝቷል ። ቀጥሎም በ measurement & evaluation ትምህርት ሁለተኛ ዲግሪውን ተቀብሏል ። ሦስተኛ ዲግሪውን አጠናቋል ።

ሠርቅ ዳ. '' ቆንጆዎቹ '' የተሰኘ አህጉራዊ ጭብጥ ያለው ረጅም ልቦለድ በ22 ዓመቱ አሳትሟል ። ቆንጆዎቹን የጻፈው በአራት ወር ጊዜ ውስጥ ነው ። ይሄው ተወዳጅ ስራው በሬዲዮ ተተርኮለታል። 'ጭጋግ ና ጠል '' በተሰኘው የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ውስጥ '' ብርቅዬ '' ና ''ፍርሐት'' የተሰኙ አጫጭር ታሪኮች ተካተውለታል።

ቆንጆዎቹ ከታተመ ከአሥራ አምስት ዓመት በኃላ በ37 ዓመቱ ልብ አንጠልጣይ ና በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ላይ የሚያተኩር 'የቃየን መስዋዕት' የሚል ረጅም ልቦለድ ለህትመት ብርሃን አብቅቷል ። ደራሲው 'የቃየን መስዋዕት' የሚለውን መጽሐፍ ለመጻፍ አምስት ዓመት ፈጅቶበታል ። ሠርቅ ዳ. የሚፅፋቸው ልቦለዶች አእምሮን ሰቅዞ የሚይዙ ፣ ትንፋሽ የሚያሳጥር ታሪክ ጽፎ 'ካልጨረስከኝ አልተውህም' የሚል ስሜት በአንባቢያን ዘንድ እንዲፈጠር የማድረግ ክህሎት አለው ። መጽሐፉ በልብ ሰቀላነታቸው የሚታወቁ ከመሆኑም በላይ በጥልፍልፍ ታሪክ ና በፈጣን እንቅስቃሴ የተሞላ ነው።

ሠርቅ ዳ. ፊልም የምናይ እስኪመስለን ድረስ በድርጊት የተሞላ ታሪክ መተረክ ይችላል። መጽሐፋን ስናነብ 'ትርጉም ይሆን እንዴ?' የማነበው ብለው ራስዎን እንዲጠይቁ ያደርጋሉ ። እንደ 'ኸርቪንግ ዋላስ' በጥናት የተደገፈ ሥራ ሰርቶ በመጽሐፉ ለማሳየት ሲተጋ ይታያል ። በዚህ የተነሳ ኢትዮጵያዊው 'ኸርቪንግ ዋላስ' ብለው የሚጠሩት አሉ ። ደራሲ ሠርቅ ዳ. ከቃየን መሰዋዕት መጽሐፍ በኃላ እስካሁን ድረስ በመጽሐፍ አልተከሰተም ። ''ሥነፅሁፍ እንደ ሆቢዬ ነው። ሲያሰኘኝ ሲያሰኘኝ{ ሲመጣልኝ} እጽፋለሁ '' የሚለው ሠርቅ ዳ. ከ1995 ጀምሮ ከ ድርሰት ዓለም እንደ ጠፋ ነው ። ምስሉ እንኳን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እንኳን አይገኙም ። በሚዲያ ላይ ድምፁንም ምስሉንም ተሰምቶና ታይቶ አይታወቅም ። የት ነው ያለኸው የኔ ሲግመንድ ፎሮይድ?? የኔ ኸርቪንግ ዋላስ?


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
129 views08:40
Open / Comment
2021-05-29 11:40:26
112 views08:40
Open / Comment
2021-05-29 06:15:55 ‹‹ንባብ የጀመሩ ብዙ ወጣቶች ያነበቡት መፅሐፍ ሁሉ ሲስባቸው ይኖራሉ፡፡ በየሳምንቱ እየፈረሱ ይሠራሉ፡፡ የእምነት መፅሐፍ ሲያነቡ የዓለም መፍትሄ እምነት ነው ይላሉ፡፡ የክህደት መፅሐፍ ሲያነቡ የእድገታችን ማነቆ እምነት ነው ይላሉ፡፡ የዝሙት መፅሐፍ ሲያነቡ የጥልቅ ደስታ ምንጩ ወሲብ ነው ይላሉ፡፡ ይህንንም ላገኙት ሠው ሁሉ ያውጃሉ፡፡ ከልጅነታቸው ጀምሮ ማንበብን ስላለመዱ እንደ አዲስ ሐብት ዓመል ያወጣባቸዋል፡፡ ››

(ራዕይ ያለው ትውልድ - 216)


╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
128 views03:15
Open / Comment
2021-05-28 18:00:38
ገና በማለዳ .............
ከዕልፍኙ ቀርቤ
መሻቴን ቀብቅቤ ፤
እንደተሰየምኹኝ
ከዙፋን ተሾምኹኝ
በዋንጫው ማለልኹኝ
ጽዋውን ጨለጥኹኝ
ወይን ደጋገምኹኝ ።

በቀትር ዕድሜዬ .........
ጀንበር ስትገለጥ ፣
የወይን ጣዕሙ ፣ ጥፍጥናው ጨመረ
ሥጋዬ ናወዘ ፤ አካሌም ሰከረ
ዐይኔን እንባ ሞላው ፤ ልቤ በ'ቶን ጋመ ።

በእኩለ ሌሊት ..........
በግለት ነደድኩኝ
ነድጄ ከሰልኩኝ
ከስዬም አመድኩኝ ።

አንቺ ግን ንጋቴ ........
ዐቧራ እንደኾንኹኝ ከትቢያ ወድቄ ፤
ሥጋዬን ሳልሸሻት
ነፋስ ኾነሽ መጣሽ ........
ነፍሴን አተረፍሻት
ወ...ደ...ጽ...ድ...ቅ....... ወ...ሰ...ድ...ሻ...ት።

( መነሻ ሐሳብ - ሩሚ )

ተስፋኹን ከበደ ፦ ከ የሞት ጥቁር ወተት

╭•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀:
@keney_serezoch
@keney_serezoch
╰ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ

ፍቅር አሁን !!
22 viewsedited  15:00
Open / Comment