Get Mystery Box with random crypto!

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ለማካሄድ የምርጫ ቦርድ የጊዜ ገደብ ቢያስቀምጥም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምር | DW Amharic

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ለማካሄድ የምርጫ ቦርድ የጊዜ ገደብ ቢያስቀምጥም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ እንቅስቃሴ ሲደረጉ ብዙ አይስተዋልም። የምርጫ ቦርድ እስከ ምርጫ ክልል ድረስ በመውረድ ጽህፈት ቤቶችን የማዋቀር ስራ ከክልሎች ጋር በመተባበር እያከናወነ መሆኑን አስታውቆ ነበር። የምርጫ ቦርድ እያደረኩ ነው ከሚለው ዝግጅት አንጻር በፖለቲካ ፓርቲዎች ዘንድ እንደ የምርጫ ዓመት የጎላ እንቅስቃሴ እንደማይታይ በርካቶች ይናገራሉ። ሰሞኑን ገዢው የብልጽግና ፓርቲን የሚደግፉ ሰላማዊ ሰልፎች በአብዛኞቹ የሀገሪቱ ክፍል እየተካሄዱ ነው። መንግስት« ህግ የማስከበር ዘመቻ » ካለዉ የትግራይ ጦርነት በኋላ ከትግራይ ክልል ውጭ በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል ምርጫው መደረጉ የማይቀር ይመስላል። ነገር ግን በሀገሪቱ አሁንም ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉ በስፋት ይነገራል። ከሱዳን ጋር የተፈጠረው ውጥረት ፣ታዋቂ ፖለቲከኞች መታሰር እና በሀገሪቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ሲደረጉ የነበሩ ግጭቶች መፍትሔ አለማግኘታቸዉ የምርጫዉን ዝግጅትና ሒደት ላለማወካቸዉ ዋስትና የለም የሚሉ አሉ።የናንተስ አስተያየት ምድነዉ? ምርጫውን በተመለከተ? በየአካባቢያችሁ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴስ ምን ይመስላል? ሀሳባችሁን አጋሩን።