Get Mystery Box with random crypto!

​┈┈••◉የጠፋው ሬሳ◉●••┈ ምዕራፍ ሁለት ክፍል :¨·... | Emoji feelings🦋

​┈┈••◉የጠፋው ሬሳ◉●••┈
ምዕራፍ ሁለት ክፍል
:¨·....................:¨·.



የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር)

....አናቱን ብዬ ሁለት ቦታ ልከፍለው ለራሴ ወሰንኩ፡፡ ያነሳሁትን መጥረቢያ ለነዛ ሁሉ ስቃይ መልስ መሆኑ ለኔ ነው ሚገባኝ፡፡ ከአብሯደጓቼ ጋር መጥቼ ብቻዬን ሊሰደኝ ያቆበቆበው ወይንም ደግሞ ሊቀላኝ የዳዳው ይህ ደም የጠማው መጥረቢያ ነው፡፡ የስቃዬን በትር ሚሰነዝረው ደግሞ ከፊት ለፊቴ ጀርባውን ሰቶኝ የተገተረው ጣእረ ሞት የህይወቴ ጨለማ ነው፡፡ በእጄ ፍትህ የጨበጥኩና ለፍርድ በቅንነት እንደቆመ ታማኝ የህግ ሰው የምዳኛቸውን የነፍሳት ዋይታ በደስታ የምቀይር ያህል ውስጤ ሊሰይፈው ማለ፡፡ ብምረው አይማረኝ ብዬ መጥረቢያውን ስሰነዝረው ከበስተሗላዬ "ወይኔ ልጄን" ብላ ትልቋ ሴትዮ ገፈተረችኝ፡፡

ወትሮም የሰውዬው ቁመት ረዥም ነበርና መጥረቢያውም ካሰብኩበት ማረፉ ቀርቶ ጀርባው ላይ በግራ በኩል ከትከሻው ዝቅ ብሎ አጥንቱ ላይ ተሰንቅሮ ተጣብቆ እዛው ቀረ፡፡ ክፍሉ ነግሶበት ከነበረው ፀጥታ ሰገሮ አምጦ የዋይታ ድባብ ሰፈነበት፡፡ ከትንሿ ሴትዮ ጋር እየተወረጫጩ ያውሩ እንጂ በመሃላቸው የቃል ልውውጥ አልነበረም፡፡ አልፎ አልፎ በንዴት ስትናገር ቃል ታወጣለች እንጂ ፀጥ ብሎ ነበር፡፡ሴትየዋ ስትገፋኝ በክፍሉ ካለው አንዱ ጠረጴዛ ጋር ተላተምኩኝ፡፡ በዛች ቅፅበት ተረባርበው በድኔን ለቀብር እንዳይመች አርገው ይሰነታትሩታል ብዬ ባስብም ግን ማንም የኔ ነገር ግድ አልሰጠውም፡፡ ይልቁኑ ያንን ጥልማሞት ሰይጣን ነፍሰ በላ ከስቃዩ ሊታደጉት መጥረቢያውን ለመንቀል ይውተረተራሉ፡፡ ከሱ ሚወጣውን የሲቃ ድምፅ ስሰማ በደስታ ነፍሴ ስትዘል ተሰማኝ፡፡

ቀልባቸው ከኔ አለመሆኑ ሲገባኝ በድንጋጤ እየተብሰከሰከ የነበረ ሰውነቴን አጀግኜ የሞት ሞቴን ተነስቼ ከክፍሉ ወጣሁ፡፡ አልፎ አልፎ ከሚገባው ፀዳል በቀር ከክፍሉ ውጪ ያለው ስፍራ ፅልመት ወርሶቷል፡፡ ይሄ ለኔ ግድ አልነበረውም ከዚ ሞት ካጠላበት የአረመኔዎች ታዛ በህይወት መውጣቴን ተስፋ አድርጌ ወደ ፊት መንጓዴን ተያያዝኩት፡፡

እግሬ ግን ብዙ ሊያራምደኝ አልቻለም፡፡ ክፉኛ የተመታው ከጉልበቴ በታች ያለው አካሌ እርምጃዬ በጀመረ ቁጥር በእጥፍ ስቃዬን ይበረታል፡፡ ተማርኮ ከመሞት እየሸሹ መሞት ለኔ ክብር አለው፡፡ "ቆሜማ አልሞትም አዎ አልሞትም" አልኩኝ ለራሴ፡፡ ትንሽ እንደተራመድኩ ከአንዱ ክፍል ውስጥ በሰመመን የሚያቃስት የሲቃ ድምፅ ደረሰኝ፡፡ እንደኛው እድል ዞራበት ወደ ሞቱ የገሰገሰ የገዳይ ግዳይ ሊሆን የተዘጋጀ የመስዋዕት በግ ይሆን እንደሁ ብዬ ወደ ክፍሉ ገባሁ፡፡

ነገር ግን ያየሁትን ማመን አልቻልኩም፡፡ "ባርሳ" ነበረች፡፡ ከቆመ ብረት ጋር ስለት ባለው የአንገት ሰንሰለት ታስራለች፡፡ ሁለት እጆቹ ወደየ አቅጣጫቸው በገመድ ታስረዋል፡፡ የለበሰችው ልብስ በደም ወይቧል፡፡ ለሰከንድ ተሳስታ ዝቅ ብትል አንገቷ ከላዯ ላይ ተቀንጥሶ ከወለሉ ላይ መንከባለሉ አይቀርም፡፡

ባርሳ ፍፁም ከባድ የህይወት ትግል ውስጥ ነች፡፡ ከጀርባዋ በኩል ያለው ክፍት መስኮት የሚያስገባው ወገግታ ክፍሉን አፍክቶታል፡፡ እንዴት ልረዳት እንደምችል እያንሰላሰልኩኝ ወደሷ ተጠጋሁ፡፡ ህመሟ በቀል የማይገለፅ ነው፡፡ በገመድ የታሰረ የመሰለኝ እጇ በካቦ ሽቦ የታሰረ ነበር፡፡ እጇን ሰርስሮ ወደ ውስጦ ሊዘልቅ ምንም አልቀረውም፡፡

ከእስራቱ አለፍ ብሎ ያለው አካሏ የደም ሽል ይዞ ውጥር ብሏል፡፡ ደምስሯ ሊበጠስ የሰከንድ ዕድሜ ቢቀረው ነው፡፡ ሞት አልፈለጋትም እንጄ ደጁን እየቆረቆረች ነው፡፡ የሞት መልአክ አይቶ እንዳላየ ለቁም ስቃይ ሸለማት፡፡ እንባዬ ከአይኔ መዝረብረብ ጀመረ፡፡ እንዴት አድርጌ ልርዳት እንዴትስ ላግዛት፡፡

እግሯ አካሏን መሸከም አቅቶት ይብረከረካል፡፡ እህል አይቶ ማያውቀው አንጀቷ ይንዘፈዘፋል፡፡ ዝቅ ባለች ቁጥር ወደ አንገቷ የሚሰርገው እሾህ መሳይ ስለት ያለው ሰንሰለት ነፍሷን ያስጨንቃታል፡፡ መኖር የጓጓች እስትንፋሷ እጅ አልሰጥ ብላ የዛለ አካሏን ለመኖር በሚደረግ ጦር ሜዳ ላይ አዝምታዋለች፡፡ አንድ ነገር አሰብኩኝ የታሰረችበት ቆሞ ያለው ብረት ከመሬቱ ጋር የተቸነከረ አይደለምና ከነ አካሏ ቀስ አድርጌ መሬት ላይ ለማንጋለል፡፡

ግን የእጇን እስራትስ እንዴት ልፈታው እችላለሁ፡፡ እሷ አላወቀችኝም የማወቅ ልኩ ላይ አይደለችምና፡፡ እኔ ከማልቀስ ውጪ ላረግላት የቻልኩት ቅንጣት አልነበረም፡፡ ከፊት ለፊቷ ቆሜ ለዚ ስቃይ እንደተውኳት ብታውቅ ምነኛ አምርራ እንደምጠላኝ ሳስበው ራሴን ረገምኩኝ፡፡ ብኩን ነኝ የማልረባ፡፡ የእግሬ ህመም ትንሽም ቢሆን ጋብ ብሎልኛል፡፡

ባርሳን ሳያት ሄጄ እሷ ላይ አለመጠምጥሜ ገረመኝ፡፡ ይሄን እርጋታ ከየት አመጣሁት ወይንስ ደነዘዝኩ፡፡ አሁን ከራሴጋ ሳወራ በቅጡ ማሰብ እየጀመርኩ ነው፡፡ ከድንዛዜዬ ነቅቼ ገባውን መቃኘት ጀመርኩኝ፡፡ እጇን ከፈታሗት መላ አካሏ ወደ መሬት ቁልቁል መምዘግዘጉ ነው እንደዛ ከሆነ ደግሞ አንገቷ እዛው ይቀላል፡፡ ስለዚህ ሰውነቷ ከብረቱ ጋር ተጣብቆ የሚቀርበትን ሁኔታ መፍጠር አለብኝ ስል አሰብኩ፡፡

ክፍሉ ውስጥ ካለው ከአንዱ አልጋ ላይ ቀበቶ መሳይ ማሰሪያ አገኘሁ፡፡ ወደርሷም ተጠጋሁና ከዳሌዋ ከፍ አድርጌ ከብረቱ ጋር የፊጢኝ አሰርኳት፡፡ አካሏ ከመድከሙና ከመቁሰሉ የተነሳ እያንዳንዱ ንኪኪዬ ለሷ ህመሟ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ሌላ ስንክሳር እጇ የታሰረበት ካቦ ፈፅሞ በኔ አቅም የሚፈታም የሚበጠስም አልነበረም፡፡ የአንገቷም ሰንሰለት እንደዛው፡፡

ባርሳን ፈፅሞ እዚ ጥያት አልወጣም፡፡ ከሞትንም አብረን ነው እንጂ፡፡ የታሰረችበትን ለመበጠስ የሚረዳኝን መሳሪያ ሁለቱ ሴቶች ከጣረ ሞቱ ጋር አንድ ላይ በሚሆኑበት ክፍል ውስጥ ተመልክቼዋለሁ፡፡ እናም አመጣዋለሁ፡፡

ይቀጥላል

ሀሳብ አስተያየት

እንዲቀጥል አብሮነታችሁ አይለየን​​​​​​

┄┄┉┉✽‌»‌ ✿» ‌✽‌┉┉┄┄
          
:¨·.·¨: