ሲዳማ ቡና ከኢትዮጲያ ቡና ከሊጉ መሪዎች ብዙም ሳይርቅ በ25 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ሲዳማ ቡና ጥሩ አቋም እያሳዩ ከሚገኙ የሊጉ ክለቦች መካከል ይጠቀሳል፡፡ ሲዳማዎች በሊጉ ሽንፈት ሳያስተናግዱ ስምንት ሳምንት ዘልቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ወጣ ገባ በሚል አቋም የመጀመሪያን ዙር ጨርሷል፡፡ ቡድኑ በሚጠበቀው ልክ የዋንጫ ፉክከር ላይ ተጽዕኖ መፍጠር ቢከብደውም በ20 ነጥብ 8ኛ ደረጃን ይዞ የሊጉ ወገብ ላይ ተቀምጧል፡፡ ቡናዎች በሊጉ ባደረጓቸው የመጨረሻ ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ ተስኗቸዋል፡፡ ተጋጣሚዎቹ ከተገናኙባቸው የመጨረሻ ስድስት ጨዋታዎች ውስጥ ሶስት ጊዜ አቻ ሲለያዩ ሁለት ጊዜ ኢትዮጵያ ቡና፣ አንድ ጊዜ ደግሞ ሲዳማ ቡና አሸንፈዋል፡፡ 787 views08:59