🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

34ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ..... - ጉባኤው ለሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ትላንት | ገራዶ ሚዲያ

34ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ.....

- ጉባኤው ለሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ትላንት ምሽት ተጠናቋል።

- በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ጉባኤው በቪድዮ ኮንፈረንስ ነው የተካሄደው።

- "የአፍሪካን ባህል፣ ኪነት፣ ሙዚቃ ፣ ቋንቋና ትውፊት ይዘን አፍሪካን ወደምንፈልግበት እናደርሳለን" የሚል መሪ ቃል ነበረው።

- የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ፕሬዜዳንት ፌሌክስ ቺሲኬዲ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

- አዲሱ ሊቀመንበር አዲስ አበባ ተገኘተው የAU ጉባኤ አዳራሽ ውስጥ ከቀድሞ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪካው ፕሬዜዳንት ራማፎሳ (እሳቸው ቨርቿል) ሆነው ርክክብ አድርገዋል።

- ከቻድ ሙሳ ፋኪ እንደገና የAU ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተመርጠዋል። ምክትል ኮሚሽነር የሩዋንዳዋ ዶክተር ሞኒክ Nsanzabaganwa ሆነው ተመርጠዋል።

- የአፍሪካ ሰላም ጉዳይ፣ የኢኮኖሚ ውህደት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር በአፍሪካ ማስፈን ሌሎች አፍሪካን እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮችን የሚያነሱ አጀንዳዎች ነበሩ። በዋነኝነት ኮቪድ-19 ወረርሽኝ መዋጋት፣ ክትባት ለሁሉም ማዳረስ የሚሉት ሃሳቦች ተነስተውበታል።

Via Ambassador Dina Mufti #Tikvah

t.me/geradomedia