Get Mystery Box with random crypto!

'ኢትዮጵያ ጠንክሪ!' - ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ሱሀይር አብዱረህማን ሰዎቹ እንኳን ችግር ላይ ሆነህ | ገራዶ ሚዲያ

"ኢትዮጵያ ጠንክሪ!" - ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ሱሀይር አብዱረህማን

ሰዎቹ እንኳን ችግር ላይ ሆነህ ይቅርና እንዲሁም ሰላም ሆነህ አይተውሁም። ተንኮል እና ክፋት አብሯቸው ያደገ ነው። አንተ ቤት እሳት ቢነድ እሳቱን ለማጥፋት ውሀ ስጡኝ ብትላቸው አይሰጡህም።

አሁን ግብፆች በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ያሉትን እሳቶች እንዴት አድርገን ማቀጣጠል አለብን የሚል የክፋት ቤንዚናቸውን ስለማርከፍከፍ እያወሩ ነው። የቴሌቪዥን ቻናሎቻቸውን ብትከፍቱት፤ የፌስቡክ ገፆቻቸውን ብትፈትሹ ጋዜጣቸውን ብታገልብጡት፣ ሁሉም የሚያወሩት ኢትዮጵያ አሁን ላይ በሀገር ውስጥ ችግር ስለተያዘች እንዴት እናፍርሳት/እናጥፋት እንጅ እንዴት ሰላሟን መመለስ እንዳለበት "በምን እንገዛት" የሚል፣ ሀሳብ አታገኙባቸውም። ይገርማል!

እነሱ ለኢትዮጵያ ብቻ አይደለም እንዲህ የሚከፉት፣ ሱዳንን ለሁለት ሰንጠቀዋል። ሊበያን አፍረሰዋል። ከበረሀ የፈለቀ ውሀ ወደ ፊሊስጤም መሬት እንዳሄድ በአሽዋ ደፍነዋል። በረሃብ ላይ ያሉ ፍልስጤማውያን ወደ አገራቸው እንዳይገቡ ድንበራቸውን ዘግተዋል። ኧረ ምን ተዘርዝሮ ያልቃል።

እንደለመዱት የአባይን ውሀ በብቸኝነት ለማፈስ፣ ሲሉ ኢትዮጵያ ከማፈረስ ወደኋላ አይሉም። በመካካለኛው ምስራቅና በአፍሪካ ብቸኞቹ የመድሀኒት አምራች አገር ዘመናዊ የኢንዱስትሪ አገር፣ የአትክልት አምራች አገር፣ ጠንካራ ሚሊተሪ ያላት አገር ለመሆን ሲሉ ሁሉንም ክፋቶቻቸውን፣ ካደጉበት ሴራቸው ልምድ ወስደው አይፈፅሙትም አይባልም።

ለዚህም መድሃኒቱ፣ ኢትዮጵያ ጠንካራ ሆና መታየት ብቻ ነው! የነሱን ሴራና የነሱን ማንነት ከወዲሁ ተረድቶ የነሱን ሴራና የነሱን የጥፋት አላማ ማክሸፍ የመላው ኢትዮጵያዊያን የጋራ ስራ ይሆናል።

ሰላም ለጎረቤታችን አገር ኢትዮጵያ!
ጋዜጠኛ ሱሀይር አብዱረህማን

በሱሌማን አብደላ

t.me/geradomedia