ማቴዎስ 16 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ #ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። ¹⁴ እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። ¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን #ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ_ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። 51 viewsBini Grham, 17:20