Get Mystery Box with random crypto!

ማቴዎስ 16 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን | GOD'S GOSPEL

ማቴዎስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ #ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።

¹⁴ እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት።

¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን #ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።

¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ_ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።