ስሜ አብዱልጀባር ኑራ ሲሆን የምኖረው በሂጦሳ ወረዳ 02 ቀበሌ ነው፡፡ በመዳወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ 2011 ዓ.ም በውሃ ሃብት እና ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ በዲግሪ የተመርኩ ቢሆንም በቀላሉ ስራ ማግኘት ባለመቻሌ በመኖሪያዬ አካባቢ ቤተሰቦቼን በእርሻ ስራ እያገዝኩ እኖር ነበር ፡፡ አሁን ግን ምስጋና ለለእርሻ ይግባዉና በአካባቢያቸን አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ የለእርሻ ወኪል ሆኜ በመስራት ከእርሻ ግብዓት እስከ መካናይዜሽን አገልግሎት በማቅረብ ለአርሶ አደሩ ማህበረሰብ የማይናቅ አስተዋፅዖ እያበረከትኩ እገኛለሁ፡፡ @Lershaapp 277 views07:34