2021-09-29 19:39:13
ሴት ልጅ በመፅሐፍ "ቅዱስ"
ሴት ልጅ ሰው በተሰበሰበበት መናገር አትችልም
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 14:35
ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
ሴት ልጅ ማስተማር አይፈቀድላትም
1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:12
ሴት ግን በዝግታ ትኑር እንጂ ልታስተምር ወይም በወንድ ላይ ልትሰለጥን አልፈቅድም።
ሴት ለአምላኳ እንደምትገዛ ለባልዋ መገዛት አለባት
ኤፌሶን 5፣22
ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ
ሴቶች ደካማ ናቸው
1ኛ ጴጥሮስ 3፥7
ባሎች ሆይ፥ ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ
ሴት ልጅ ከባልዋ ብትፋታ እንኳን ባልዋ በህይወት እስካለ ድረስ ሌላ ባል ማግባት አትችልም
ወደ ሮሜ ሰዎች 7:2-3
ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች።
ከባልዋ የተፋታች ሴትን ማግባት አይቻልም
[የማቴዎስ ወንጌል 19:9]
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን ፈትቶ ሌላዪቱን የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ያመነዝራል አላቸው።
ሁከተኛ ናት
መጽሐፈ ምሳሌ 9:13
ሰነፍ ሴት ሁከተኛ ናት፤ አሳብ የላትም፥ አንዳችም አታውቅም።
ጠበኛ ሴት
መጽሐፈ ምሳሌ 21:9
ከጠበኛ ሴት ጋር በአንድ ቤት ከመቀመጥ በውጪ በቤት ማዕዘን ላይ መቀመጥ ይሻላል።
በምድረበዳ መቀመጥ ይሻላል
መጽሐፈ ምሳሌ 21:19
ከጠበኛና ከቍጡ ሴት ጋር ከመቀመጥ በምድረ በዳ መቀመጥ ይሻላል።
የሚያንጠባጥብ ቤትና ጠበኛ ሴት
መጽሐፈ ምሳሌ 27:15
በዝናብ ቀን የሚያንጠባጥብ ቤትና ጠበኛ ሴት አንድ ናቸው፤
ሴት ስትወልድ ትረክሳለች። የወለደችው ሴት ልጅ ከሆነ ደግሞ ከወንድ ለእጥፍ ቀናት ትረክሳለች
ኦሪት ዘሌዋውያን 12:2,5
ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው። ሴት ብታረግዝ ወንድ ልጅም ብትወልድ፥ ሰባት ቀን ያህል የረከሰች ናት፤ እንደ ሕመምዋ መርገም ወራት ትረክሳለች።
ሴት ልጅም ብትወልድ እንደ መርገምዋ ወራት ሁለት ሳምንት ያህል የረከሰች ናት፤ ከደምዋም እስክትነጻ ድረስ ስድሳ ስድስት ቀን ትቀመጥ።
ሴት ልጅ ኃይድ ላይ በምትሆንበት ጊዜ እርኩስ ነች
ኦሪት ዘሌዋውያን 15:19-28
[19]፤ ሴት ፈሳሽ ነገር ቢኖርባት በሥጋዋም ያለው ፈሳሽ ነገር ደም ቢሆን፥ በመርገምዋ ሰባት ቀን ትቀመጣለች፤ #የሚነካትም ሁሉ እስከ ማታ ድረስ #ርኩስ ነው።
[20]፤ መርገምም ስትሆን የምትተኛበት ነገር ሁሉ #ርኩስ ነው፤ የምትቀመጥበትም ነገር ሁሉ ርኩስ ነው።
[21]፤ መኝታዋንም የሚነካ ሁሉ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም ድረስ #ርኩስ ነው።
[22]፤ የምትቀመጥበትንም ነገር ሁሉ የሚነካ ሁሉ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም #ርኩስ ነው።
[23]፤ በመኝታዋም ላይ ወይም በምትቀመጥበት ነገር ላይ ቢሆን ሲነካው እስከ ማታ ድረስ #ርኩስ ነው።
[24]፤ ማንም ከእርስዋ ጋር ቢተኛ መርገምዋም ቢነካው፥ ሰባት ቀን ርኩስ ነው፤ የሚተኛበትም መኝታ ሁሉ ርኩስ ነው።
[25]፤ ሴትም ከመርገም ቀን ሌላ ደምዋ ብዙ ቀን ቢፈስስ፥ ወይም ደምዋ ከመርገምዋ ወራት የሚበልጥ ቢፈስስ፥ በመርገምዋ ወራት እንደ ሆነች እንዲሁ በፈሳሽዋ ርኵስነት ወራት ትሆናለች፤ ርኩስ ናት።
[26]፤ ደምዋም በሚፈስስበት ወራት ሁሉ የምትተኛበት መኝታ ሁሉ በመርገምዋ ጊዜ እንደ ነበረው መኝታ ያለ ይሆንባታል፤ የምትቀመጥበት ነገር ሁሉ እንደ መርገምዋ ርኵስነት ርኵስ ነው።
[27]፤ እነዚህንም ነገሮች የሚነካ ሁሉ ርኩስ ነው፤ ልብሱንም ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም ርኩስ ነው።
[28]፤ ከፈሳሽዋም ብትነጻ ሰባት ቀን ትቈጥራለች ከዚያም በኋላ ንጹሕ ትሆናለች።
"ቅዱስ" የተባለ መፅሐፍ ሴትን ልጅ በዚህ ደረጃ ሲያዋርዳት ሲያሳንሳት ማየት ስቅጥጥ ይላል። ለመሆኑ ክርስቲያን ሴቶች ይህንን ታውቁ ይሆን?
https://t.me/Zelebet
810 views16:39