🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ

Channel address: @bewketuseyoum19
Categories: Courses & guides
Language: English
Subscribers: 135.71K
Description from channel

➲የበእውቀቱ ስዩም ፈገግታም እውቀትም የሚሰጡ ወጎች ፣ ግጥምች እና የተለያዩ ፀሀፊዎች የስነጽሑፍ ስራዎች የሚቀርብበት ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
@bewketuseyoum19
Buy ads: https://telega.io/c/bewketuseyoum19
For your comment,feedback and promotion @Bewketuseyoum2bot
Thank you!

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 135

2022-03-02 08:58:32 #ሐበሻ_በአድዋ

የሚንቀለቀል የነጭ እግር፣
ትዕቢት ያረገዘ የቀላ የሰው ዘር፣
ጣሊያን መጣ እሬሳ ሊያስቆጥር።

መትረየስ አዝሎ ሊገል ሊያስፈራራ፣
ሀበሻንም ጥሎ ኢትዮጵያን ሊመራ፣
ጥቁር መሬት ገባ ፊቱን እያበራ።

እንኳንስ ሀበሻ ኢትዮጵያን ሊሰጥ፣
ይሰማ የለም ሆይ ለነፃነቱማ አሟሟቱን ሲመርጥ።

የነጩ መሳሪያ ግንባሬን ስቶ ጀርባዬን ከመታ፣
አትቁጠሩኝ እኔን ከሬሳዎች ተርታ።

ማለቱን መች ሰማ ሲፎክር ሲሸልል፣
ቅኔ ሲደረድር ቃላት ሲፈለፍል፣
ወኔ ሲቀሰቅስ ንዴት ሲያገነፍል።

ጣልያን ገና ፃዲቋን ሀገር እንደረገጠ፣
ልቡ በፍርሀት ተንቀጠቀጠ።

ሀበሻ እንኳንስ በአዋጅ ውጊያ ተዘጋጅቶ፣
ጦርሜዳው አድዋ ኑ ተብሎ ተጠርቶ፣
ድሮም መራራ ነው ይሄዳል ተነስቶ።

ታዲያ በዚያ ቦታ በተራሮች ጥግ፣
በአድዋ ሜዳ እሳት ሲንብገቦግ፣
ሀበሻ እሳቱ ነጩን አመድ ሲያደርግ።

ትንቅንቅ ሲነግስ ቦንብ ሲፈነዳ፣
አቧራ ሲነሳ መሬት ደም ሲቀዳ፣
ባለፈረስ ሲያፈርስ የብረት ግድግዳ።

ድል አየች አድዋ በሀገር በቦታዋ፣
ጊዮርጊስ ሲደርስ ክቡር ተዋጊዋ፣
ከበረች ኢትዮጵያ ሸሸ ወራሪዋ።

ጣሊያን ከሰመ ፈሰሰ ሀሞቱ፣
ሀበሻም ድል ነሳ በደም በታቦቱ፣
ቀልድ መች ያውቅና በኢትዮጵያ በርስቱ።

[#ገጣሚ_ሄኖክ_ፀጋዬ]
#ለወዳጆ ያጋሩ #ሼር #ሼር
መልካም ዝክረ አድዋ 126 ፻፳፮


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
1.3K viewsAbela, 05:58
Open / Comment
2022-03-01 16:21:56 ፈረስ ሲያስገመግም፣ጦር ጎራዴው ሲፋጅ ፣ተዘከር አድዋ
ሰው በነጻ ሊኖር ሰው እየተሰዋ!

አድዋ ትናንት ነው ፣ ዛሬ ነው ፣ነገ ነው
የእድሜ ዘመን ጸጋ ከአያት የወረስነው

አድዋ ታሪክ ነው አድዋ ተራራ
ባንድ የዘመተበት ሰው ከፅላት ጋራ!

አድዋ "እምነት ነው" የሰማዕት ገድል
ስጋ ብቻ አይደለም መንፈስም ሰው ጥሏል!

አድዋ "ሸማ ነው" ጠቢብ ያሳመረው
ክፉ የማይፍቀው ዘመን ያላስረጀው!

አድዋ ኩራት ነው ሰው የመሆን ክብር
በጥቁር ተሰብሯል ነጭ የገራው ቀንበር!

አድዋ ጸሀይነው ሰው ያነጸው ጮራ
ከሮም ብርሀን ነጥቆ ለጦብያ ያበራ!

አድዋ "በትር ነው" ጠላት የሞተበት
"አልሞት ባይ ተጋዳይ" ድል የከጀለበት!

አድዋ "ቅርስ ነው" አድዋ ስንክሳር
ለኛ ጆሮ ሀሴት ለዚያ ጎራ ሀሳር!

ይናገር ምኒሊክ ይናገር ይመስክር
እምነትና ግዛት እንዴት እንደነበር!!!

ክብር በዓድዋ ተራራ በባዶእግራቸው በጦርና ጎራዴ ዘመናዊ መሳርያን ከታጠቀ ወራሪ ጋር ታግለው ዛሬ በየ ፊናችን "አድዋ አድዋ..." እያልን እንድንዘምር ዋጋ ለከፈሉልን ለኒያ ጽኑና ጀግኖች አባቶቻችን ይሁን!!!

እንኳን ለ 126ኛው የጥቁር የነጻነት ቀን አደረሳችሁ!!!

መልካም የዓድዋ ድል!

(ታደሰ ደምሴ)
@Maryam21161

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.5K viewsAbela, 13:21
Open / Comment
2022-03-01 15:30:39 ወይ መምህር ሊያሳድረን ነው እንዴ?
ጨርሻለሁ ካለ ግማሽ ሰዓት አልፎታል
ምሳሌያዊ አነጋገር ምን ማለት ነው? ጥያቄው ለ'ኔ ነበር።
ኸ ምሳሊያዊ አነጋገር ያው በስነ-ምግባር የታነፀ ንግግር ማለት ነው ከማለቴ ጥግ ላይ 'ምትቀመጠው ፅዮን ከጓደኛዋ ጋ ከትከት ብለው ሳቁብኝ።
መምህር ተበሳጩ ምን ማለት ነው ምሳሌያዊ አነጋገር ላንቺ ፂዮን?

ም ሳ ሊ ያ ዊ አ ነ ጋ ገ ር ማ ለ ት ቲ ቸ ር ዬ

ምኗ ሞዛዛ ናት አሉ መምህሩ እንደውም ከክፍሌ ውጡልኝ ውልፍጥ።

ተማሪዎች ምሳሊያዊ አነጋገር ማለት በማህበረሰቡ ልማዳዊ ስምምነት መሰረት የሚፈጠር በቁጥብ'ና ምርጥ ቃላት ባ'ጭሩ የሚነገር የተጨመቀ ጥልቅ ሀሳብን የያዘ የስነ-ቃል አይነት ነው።

መሀል ሰፋሪው ማስረሻ ለመጠየቅ እጁን አነሳ እሺ ማስረሻ ጠይቀኝ።
መምህር ምሳሌያዊ አነጋገርን ለመግለፅ ምሳሌያዊ አነጋጋር አጥተው ነው እንዲህ ያረዘሙት?
እቺ ባቄላ ካደረች አሉ መምህር በየነ ....ኸረ እንደውም ውጣልኝ።

በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ከአስር ሰው በላይ ከክፍል አውጥተው የቀረነው ጥቂት ነን። ተማሪዎች የምሳሊያዊ አነጋገር ምሳሌዎች ፅፍላቹሀለው በማስታወሻ ደብተር ላይ ያዟቸው ይመጣሉ ፈተና ላይ ፃፉልን።

- ቀን የሰጠው ቅል ዲንጋይ ይሰብራል
- ከእብድ አጠገብ ዲንጋይ አይወረወርም
- ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል
- ተመካክረው የፈሱት ፈስ አይሸትም።

ሁላችንም እየፃፍን ነበር ጨርሻለሁ ሲሉን ግን አሁን 'ምናርፈውን ሳይሆን ከሰዓት ሚንገላጀጁብን ነገር ያስጨንቀኛል። ለነገሩስ በኔ አልተጀመረ ዛሬ ላይ ማግኘቱን ሳይሆን የነገን ማጣት ስንቱ አይደል እያሰበ ሚጨነቀው? መምህሩ አሁን መጨረሱ ሳይሆን ቡሀላ መጀመሩ ነው 'ሚያስጨንቀኝ።

ሁሉም ወደቤቱ እየገባ ነው እኔና ጓደኞቼ ግን የለመድናት ነገር ስላለች ወደየቤታችን አንገባም። የዛን ቀን ከቤት አንዳችን አንዳችን ቤት 'ንደምንሄድ እናስፈቅዳለን። ብር ፈላልገን ወደ ለመድንበት እንሄዳለን። በያይነታችን በልተን ፣ ለውዝ ጠጥተን ፣ ስኳር ድንች በልተን ወደ ከሰዓቱ ክፍለ ጊዜ እንመለሳለን። የከሰዓቱ ትምህርት ቶሎ ነው 'የሚጀምረው ጥግግብ ብለን ክፍል ገባን።

ተስብረው 'ንኳ በክራንች ይመጧታል እንጂ መምህር በየነ እንኳን ሊቀሩ ሽራፊ ሰከንድ አያረፍዱም።

ክፍል ገቡ ስነ-ግጥም ብለው በዝርዝር ከፃፉ ቡሀላ ማስረዳት ጀመሩ። መከታተል እየከበደኝ ነው። ሆዴ ላይ ደስ የማይል ስሜት እየተሰማኝ ረብሾኛል። ጓደኞቼንም እንደዛው። እኩል ታመናል አናስፈቅድ ነገር ለሶስታችንም እሺ አይሉም። ከጓደኞቼ ባህርይ ምወደው አስተዋይነታቸውን ነበር እናም አንድ የተቀደሰ ሀሳብ አመጡ ጠዋት ከተማርነው ጋርም ስለሚደጋገፍ ሙሉ በሙሉ ሀሳቡን ተቀበልነው። መፍትሔውም ሰራ መሰለኝ ህመማችን ለቀቅ አደረገን በአንፃሩ ግን መምህሩ ማስተማሩን ትተው እያነፈነፉ ነው።
ማነው የፈሳው? አሉ በሀይለ ቃል ለካ ምሳሌያቸው'ና የጓደኞቼ ምክር ጉድ ሰርቶን ኑሯል። እንዳይሸት ብለን ክፍል ውስጥ ተመካክረን ብንፈሳም ክፍሉን ፈንጂ ላይ ጣድነው።

ማን ነው ልክ?
ትምህርቱ?
ምሳሌው
እኛ
ፈሱ?
መልሱን ባላውቀውም።

ተመካክረን የፈሳነው ፈስ ከመሽተት አልታደገንም

ናታን ኤርሚያስ
@UniqueDy

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.9K viewsAbela, edited  12:30
Open / Comment
2022-03-01 12:01:39
ኢትዮጵያውያን የድል እንጂ የነጻነት በዓል አናውቅም!
እንኳን ለ126ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.5K viewsAbela, edited  09:01
Open / Comment
2022-03-01 08:55:26 #የሊስትሮ_እቃዬ
(በቴዲ አፍሮ)

ርሀቤ ቢከሰኝ ~ ባዶ ሆዴን አይቶ
አፌ መሰከረ ~ ችሎት ላይ አዛግቶ
በህይወት ፍርድ ቤት
የተሾሙት ዳኛ ~ መፃፉን ሲገልፁ
ያልሰራ አይብላ ~ ይል ነበር አንቀፁ
ይህንን ስትሰማ
ፈጥና መጣችና ~ ሆና ጠበቃዬ
ከፍርድ አዳነችኝ ~ የሊስትሮ እቃዬ
እኔም እሱዋን ይዤ
አንገቴን ለስራ ~ ጎንበስ እንዳረኩት
ችግሬን በብሩሽ ~ ሲጠረግ አየሁት
የኩራቴን በትር
ወርውሬ ስጥለው ~ ከጄ ላይ ወደዛ
እንኳን የሰው ጫማ ~ የኔም ፊቴ ወዛ
ካመታት ቀጠሮ
ከጊዜ በኃላ ~ የዋለው ችሎት
ጥረቴን አየና ~ ቢፈርድልኝ ሀብት
ከትቢያ ተነስተው ~ እንዲሉ ከማማ
እኔም በተራዬ
ከላይ ተቀምጬ ~ አስጠረኩኝ ጫማ
እንግዲህ አዝናለው
ባለውለታዬ ~ ክብሬ ነሽ እያልኩዋት
ከታች ያነሳችኝ
የሊስትሮ እቃየን ~ ከላይ እረገጥኳት
እንግዲህ አዝናለሁ
ውድዋ…………… የሊስትሮ ዕቃዬ
ምንም እንኩዋን ~ ብትሆኝ ባለውለታዬ
በጫማ ስረግጥሽ ~ አይክፋሽ ግድ የለም
ባታውቂው ነው እንጂ
ለዋለላት ሁሉ ~ እንደዚህ ናት አለም
~||~

ከ ቴዎድሮስ ካሳሁን (Teddy Afro)

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
683 viewsAbela, 05:55
Open / Comment
2022-02-28 18:52:35 ርዕስ:- መፅሄተ ጥበብ ወዕፀ ደብዳቤ
ደራሲ:- ድድቅ ወልደ ማርያም
ዘውግ:- ስነ-ምርምር(የኢትዮጵያ ነባር እውቶች)
የገፅ ብዛት:- 295
ዓ.ም:- 2ተኛ እትም 2013

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.3K viewsBewketu, edited  15:52
Open / Comment
2022-02-28 16:53:22 ከምንጭሽ ውሀ ስር
ለመቅዳት ስታትር፣

አንገቴ ሲል ዘንበል
በደጃፍሽ በኩል፣

ተጠምቼ ስግት
የተፈጥሮን ፍንክት፣


ሰው ሆኖ ሰው መስራት
ነፍሴን ከስጋዬ ነጥለሽ ሰወርሻት።


አወይ መታደልሽ!!

ቅዱስ አርዮስ

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.1K viewsAbela, 13:53
Open / Comment
2022-02-28 15:19:13
3.1K viewsAbela, 12:19
Open / Comment
2022-02-28 12:06:25 ሰይጣንን አሳየኝ ይለኛል ፈላስፋ
ሰይጣንን ላሳየው በብርቱ ሳይለፋ!
......ይኸው አንድ አዝማሪ
እሱን የሚቀበል ብዙ ብዙ ውሪ
ብዙ እስክስተኛ
ብዙ ዳንኪረኛ
ከባሏ የሰረቀች አንዲት ቧልተኛ ሴት
አብሯት የሚገኝ ወንድ የማይፈራ ቅሌት
"ጥቁር ነው ጠይም ነው እንደ ኑግ የወዛ
አብረሽው እደሪ አትይው በዋዛ"
የሚል ዘፈን
"ቀይ ነች ቀይ ዳማ ብርቱካን መሳይ
እሷን ትለቅና እኔን እንዳታይ.. ."
የሚል ሌላ ግጥም
እሱን እየሰማ ዝሙት የሚያጣጥም
ብዙ ብዙ መንጋ...
እንደዚህ ሲሆን ነው ሰይጣን የሚገለጥ
በሰው ልጆች ስጋ!

(ሚካኤል .አ)

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.9K viewsAbela, 09:06
Open / Comment
2022-02-27 14:55:06 ነግሬሽ ነበረ

ሴት ክብሯን ረስታ ፣ ጭኗን እንዳታምነው
ሁሉን ያጣል ብዬ ፣ የሁሉም የሆነው!!!

ነግሬሽ ነበረ
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ትንሽ ስትዘነጊኝ ፣ ብዙ እንደማስብ!!!

ነግሬሽ ነበረ... ባትሰሚኝም እንኳ
ሳሙና ነው ብዬ ፣ የቆንጆ ሴት መልኳ
እድፋም ስሜቶችን...
አሽታ ስታነፃ ፣ ያበቃል ታሪኳ!!!

ነግሬሽ ነበረ
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ...
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ እናቶች አይደሉም
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።

ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯን ስትጥል ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡

ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።

ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።

ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይመኟታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!

በላይ በቀለ ወያ እንደፃፈው

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.1K viewsAbela, 11:55
Open / Comment