2021-07-02 18:14:40
#7......
አባት ሴት ልጁን የመከረው ምክር (1)
ይህ አባት ለሴት ልጁ የመከረው ምክር ነውና በማስተዋል አንብቡት !
ወጣት ሴቶች ልጆች እንዲጠነቀቁ
ወላጆች ሴቶች ልጆቻቸውን እንዲመክሩ ይረዳችኃልና !
ወድ ልጄ በምድር እንድትኖሪበት የተሰጠሽን ሕይወት ዳግመኛ ተመልሰሽ አትኖሪበትም! የተፈጠርሽበትን ዓላማ ከፈጠረሽ አምላክ ጠይቂ! በተሰጠሽ ዘመን ለፈጠረሽ አምላክ ፈቃድ ተገዢ !
☞ ሴት ልጅ ውድ ነች ርካሽ ብትሆን ለውዷ ቤተክርስቲያን በምሳሌ አትሰየም። በእግዚአብሔር ላንቺ የተመዘነው ዋጋ የክርስቶስ ደም ነው ራስሽን ማየት ያለብሽ እግዚአብሔር በሚልሽ እንጂ ሰይጣንም፣ ሰውም፣ ሁኔታም፣ በሚገልጽሽ ማንነት አይደለም። በእግዚአብሔር እንደተወደደች እንደ ውድ ዕንቁ ሴት ራስሽን ቁጠሪ፤
☞ እግዚአብሔር በልጁ ሞት ሕይወት የሰጠሽ የከበርሽ ልጁ ነሽ!
☞ እግዚአብሔር በዓላማ ፈጥሮሻል!
☞ ከእግዚአብሔር ሐሳብ ወደ ግራም ወደ ቀኝም እንዳትይ ተጠንቀቂ!
☞ በሰይጣንና በሰው የሚሰጥሽን መደለያ ፈጽሞ አትቀበይ ወጥመድ ነውና!
☞ ክብርሽ ስኬትሽ ደስታሽ ያለው በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ነው!
☞ ለገንዘብ ራሳቸውን የሸጡትን ምክር አትስሚ! ለሁለት ጌቶች መገዛት አትችይምና! አምላኬ ገንዘብ ሳይሆን እግዚአብሔር ነው በያቸው!
☞ ሁል ጊዜ ነፍሱን ሰጥቶ ያዳነሽን ጌታ ፍቅር አስቢ!
☞ የእግዚአብሔርን የፀጋ ክብር በሙላት ይግባሽ፤
☞ ሰይጣን በላከው ተራ ወንድ አትሸወጂ ስላንቺ ያለው እይታ ከቤት ዕቃ አያልፍምና! (የቤቱን እቃ አሟልቶ አሁን ደግሞ ሚስት ብሎ ከሚያቅድ ነገ እንደ ቁምሳጥን፣አንደ መኪና የቤት እቃ አድርጎ ሊቆጥርሽ ከሚችል እይታው ከጠበበ ወንድ ተጠበቂ)፤
☞ እግዚአብሔር ፀጋውንና የክርስቶስን ልብ ሰጠን እንጂ ለእባብ የሚስቅ የሄዋንን ልብ አልሰጠንምና የቀረበሽ ወንድ ሁሉ ያንቺ አይደለምና ተጠንቀቂ።
☞ ፍቅር የዘኝ ብሎ ለሚፈጥነውም ረጋ በል ብሎ መመርመር ይገባል። ወዲያው አፈቀርኩ አበድኩ ነደድኩ ብሎ የሌለን አለም ታሪክ ዲስኩር ከሚቀድ ወንድ ተጠበቂ ተጠንቀቂ ውድቀትሽን ስብራትሽን ሐዘንሽ ለማፈጠን ከሰይጣን የተላከ የስሜት ፈረስ ጋላቢ ሊሆን ይችላልና።
☞ አበድኩ አፈቀርኩ ብሎ ኃላ የጥላቻ ቁንጮ የሆነውን አሲድ ከሚደፋ ወንድ ጋር ህብረት አታድርጊ አሲድ ባይደፋም በእርኩሰቱ ወደ ሲኦል የሚመራሽ ከዚያ ይብሳልና ተጠበቂ !
☞ ከማታውቂው መልአክ የምታውቂው ሰይጣን ይሻላል አየተባለ ከሚደሰኮር ተረት ራቂ ለሞትና ለጥፋት የሚያዘጋጅ ነውና።
☞ ይልቅ ለፈጠረሽ አምላክ ለእግዚአብሔርን የተሰጠ እውነተኛ ወንድም ከእግዚአብሔር እጅ ለመቀበል ጸልይ ከአምላክሽ ጋር የጠበቀ ሕብረት ይኑርሽ! በጸሎት በአምልኮ በቃል ጥናት በመንፈስ ቅዱስ ሙላትና ምሪት የተቃኘ ሕይወት ይኑርሽ!
☞ የተፈጠርሽበትን ዓላማ ለማሳካት ጌታን በሚያስከብር ሕይወት የአገልግሎት ጸጋሽን በመለየት አገልግይ!
☞ የሚገርመው ጌታ በውስጥሽ ያስቀመጠው የሚገርም የተዳፈነ ፀጋ አለሽ በጸሎት በቃሉና በመንፈሱ ሙላት ይገለጣልና ቀድሞ ከነበረሽ ይልቅ በጌታ ፊት ወድቆ የመጮህ ጊዜ ይብዛልሽ!
☞ ጸጋው በተገለጠ ጊዜም ለሰጪው ክብር በማብዛት በስርዓት ወደ መድረክ ይዘሽው ውጪ ለብዙዎች መዳን ምክንያት ትሆኛለሽና!
☞ በትንቢት ቃል አትታሰሪ/ትዳር/ አትመስርቺ ለነብይ የነገረው አባትሽ እግዚአብሔር ከሆነ ላንቺ በቀጥታ ይነግርሻል ልጁ ነሽና እንደ ነጎድጓድ የሚነገር ልሳን አትፍሪ አትደንግጪ!
☞ አንቺ ልባም ሴት ልጅ ነሽ የክርስቶስ ልብ ያለሸ፤
☞ አንቺ ከመውለድ ልጅ ከማሳደግ ንብረት ከመሰብሰብ ያለፈ መለኮታዊ ፕሮግራም ያለብሽ በደሙ የተገዛሽ ዕንቁ ልጁ ነሽ!
☞ የአምላክሽ ዋና ዓላማና ግብ ማግባት ብቻ አይደለም ለዘላለም ሕይወት ክብር በክርስቶስ መመረጥሽ እንጂ! በምድር ከሚሆንልሽ እና ከሚደረግልሽ ያለፈ ክብር አለሽ!
☞ የሰርጉ ሆታ ጭፈራ እልልታና ሽብሸባ የአንድ ቀን ነው። በክርስቶስ የተዘጋጀው ክብር ግን የዘለዓለም ነው!
☞ በአምላክሽ የታሰበልሽን ግብና የተሰጠሽን ተስፋ አስቢ!
☞ በጊዜው የሚመጣ ክብርሽ የሚሆንልሽ የትዳር አጋር ዘውድ የምትሆኚለት ወንድ በእግዚአብሔር እንደተወሰነልሽ አስቢ፤
☞☞☞ ይህ ከሆነ በእውነት ልባሟ ሴት አንቺ ነሽ ! ተባረኩልኝ።
sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ
@Gaggeessummaa
@Gaggeessummaa
ᴊᴏɪɴ
1.6K viewsGetu Abera✟, 15:14