Get Mystery Box with random crypto!

AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር

Logo of telegram channel ashabuleyamine — AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር A
Logo of telegram channel ashabuleyamine — AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር
Channel address: @ashabuleyamine
Categories: Uncategorized
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 7.32K
Description from channel

https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q
Telegram _Join
http://t.me/AshaBuleyamine
Twitter
https://twitter.com/AshabuleYamlne?s=09
Facebook page
https://www.facebook.com/Ashabuleyamine/
Website
http://ashabulyemin70.blogspot.com

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


The latest Messages 10

2022-02-15 16:42:13 من أكثر قصص القران رعبا !!!

በቁርኣን ውስጥ ከሚያስፈሩ ታሪኮች መካከል አንዱ

هي قصة أصحاب السبت لو تدبرت القصة بعقلية ايامنا هذه ستشعر انهم لم يرتكبوا جرم كبير

የአስሃቡ-ሰብት ህዝቦች ታሪክ ነው ታሪኩን እንዲያው በአቅል ካሰብነው በእኛ ዘመን ባለው ሁኔታ ጋር ካነጻጸርነው ያን ያህል ትልቅ ስህተት አልሰሩም የሚል ስሜት ይሰማሃል ..!

امرهم الله الا يصطادوا يوم السبت

አሏህ እንዲህ በማለት አዘዛቸው ቅዳሜ ቀን አሳ እንዳያጠምዱ በማለት አዘዛቸው ።

وما حدث ان السمك اصبح يغيب طوال الاسبوع ويأتي فقط يوم السبت

የተከሰተው ክስተት ደግሞ አሳዎቹ ሳምንቱን ሙሉ ይጠፉና ቅዳሜ ቀን ብቻ ይመጣሉ ።

أما ما قاموا به ليس الاصطياد يوم السبت الذي حرم عليهم بل كانوا فقط يلقون شباكهم يوم الجمعة ليلا ثم يسحبونها يوم الاحد صباحا

እነርሱ ይህን ባዩ ጊዜ መላ የሰሩትማ መላ ፈጠሩ የፈጠሩትም መላ አሏህ የከለከላቸውን ቅዳሜን ቀን አሳ ላለማጥመድ በሚል ጁመዓ ምሽት የአሳ ማጥመጃ መረባቸውን ይዘረጋሉ ከዛም ቅዳሜን የተከለከሉበትን ቀን አሳልፈው እሁድ ቀን ጠዋት መረቡን አሳ ያጠመደ ሲሆን ያነሳሉ ..!

لو فكرت فيما فعلوه بعقلية اليوم ستجد انهم لم يرتكبوا شيء كبير.

አሁን ባለው አስተሳሰብ በእኛ አቅል በዚህ ዘመን አስተሳሰብ ካሰብነው ትልቅን ወንጀል ያልሰሩ ሆነው ታገኛቸዋለህ ።

لكن الله غضب عليهم و لعنهم يعني أخرجهم من رحمته وجعلهم قردة خاسئين.

ነገር ግን አሏህ ተቆጣባቸው እረገማቸውም ጭምር ከእዝነቱም አራቃቸው የተዋረዱ ሲሆኑ ወደ ዝንጀሮነትም ቀየራቸው ።

وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ الَّذِينَ اعْتَدَوْا مِنكُمْ فِي السَّبْتِ فَقُلْنَا لَهُمْ كُونُوا قِرَدَةً خَاسِئِينَ

(አል-በቀራህ - 65)
እነዚያንም ከእናንተ ውስጥ በቅዳሜ ቀን (ዐሣን በማጥመድ) ወሰን ያለፉትንና ለነሱ «ወራዳዎች ስትኾኑ ዝንጀሮዎች ኹኑ» ያልናቸውን በእርግጥ ዐወቃችሁ፡፡

كل هذا لانهم التفو وتحايلوا على اوامر الله سبحانه وتعالى

ይህ ሁሉ የሆነው የላቀውን አሏህን ጥራት ይገባውና ውሳኔ ትእዛዝ በስልትና በብልጠት ብልሃትን ዘዴኔ ዘይደው ለመሸወድ በመሞከራቸው ነው ።

كم منا اليوم يعيش بعقلية التحايل والالتفاف حول اوامر الله الصريحة والواضحةالربا اصبح فائدة.والرشوة اكرامية والخمر اصبح مشروبات روحيه والعياذ بالله والنميمه اصبحت ما نحبش نسكت على الغلط والعري حرية،

ዛሬ ላይ ታድያ ስንቶቻችን ነን በብልጠት በብልሃት በእጅ አዙር በአሏህ ትእዛዛት ላይ ድንበር የምናልፈው ግልጽ የሆነውን ትእዛዙን የምንጥሰው ሪባ ( ወለድን ) ጥቅም ተባለና ስሙ ተቀየረ ረሽዋ ግቦ ደግሞ ኢክራሚያ የአክብሮት ግብዣ ተብሎ ስሙ ተቀየረ የኸምር መጠጥ ደግሞ (ሸርቡ ረውሃኒይ) የነፍስ መጠጥ ተብሎ ተቀየረ ወነኡዙ ቢላህ በአሏህ እንጠበቃለን ሃሜትንም ስህተት አይተን ዝም አንልም በሚል የሃሳብ ነጻነት ነው በሚል ስሙ ተቀየረ ።

ومن لا يصلي يقول الدين معاملة والايمان في القلب. والذي يجمع الصلاة كلها قبل ان ينام والحجاب الذي اصبح موضة

የማይሰግድ ሰው ደግሞ ዲን መኗኗር ነው ኢማን በልብ ነው ሌላው ከመተኛቱ በፊት ሶላቶቹን ሁሉ ይሰበስባቸዋል ሂጃብ ደግሞ ፋሽን ሆነ ።

والجهر بالسوء الذي نراه كل يوم في الواقع و المواقع و تحرش وافعال واقوال لاترضي الله

አሁን ላይ በግልጽ በምንመለከተው በዋቂኡም በየሶሻል ሚዲያውም የከፉ ንግግሮች ጾታዊ ትንኮሳና የመሳሰሉ አሏህን የማያስደስቱ የሆኑ ንግግሮች ።

و...المصيبة ان يكون ربنا غاضب علينا او حتى خارجين من رحمته ونحن لا نشعر بل ونعتقد اننا أولياء الله الصالحين.

የከፋው ከባዱ ነገር ደግሞ አሏህ የተቆጣብን ሲሆን ከእዝነቱም የራቅን ስንሆን እኛ ይህንን የማናውቅ መሆናችን ነው በል እንዲያውም እኛ የአሏህ ወሊዮች ወዳጆች የሱ ቅርቦች እንደሆንን እናስባለን ።

اما آن الاوان ان نتعامل مع ربنا ك رب عظيم يأمر فيطاع-الله يقول :

ጊዜው አልደረሰምን? ከጌታችን ጋር የላቀውን ጌታ ባዘዘን ነገር ላይ በሙሉ መዋረድ በመታዘዝ ታዛዥ ባሮች የምንሆንበት ጊዜ አልደረሰምን? አሏህ እንዲህ ይላል:-

مَّا لَكُمْ لَا تَرْجُونَ لِلَّهِ وَقَارًا

(ኑሕ - 13)
ለአላህ ልቅናን የማትሹት ለእናንተ ምን አላችሁ?

ويقول: እንዲህም ይላል

(وما قدروا الله حق قدره)
ተገቢ ክብሩን አላከበሩትም፡፡

ويقول:እንዲህም ይላል

(ولو انهم فعلوا ما يوعظون به لكان خيرا لهم

እነርሱም በእርሱ የሚገሰጹበትን ነገር በሠሩ ኖሮ ለነሱ መልካምና (በእምነታቸው ላይ) ለመርጋትም በጣም የበረታ በኾነ ነበር፡፡

(استقيمواينصلح حال الأمة ويرفع الله عنكم البلاء لهم)

ቀጥ በሉ የኡማው ሁኔታ ይስተካከል ዘንድ አሏህም በላውን ከላያችን ላይ ያነሳልን ዘንድ ።

اللهم صل وسلم وبارك على نبيناوحبيبنا محمد
وعلى اله وصحبه اجمعين ﷺ

https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg
833 viewsedited  13:42
Open / Comment
2022-02-15 16:41:04
460 views13:41
Open / Comment
2022-02-14 22:18:04 https://t.me/joinchat/FyB3tRsP6dZC4OwKzTbVAg

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁ

ውድ እና የተከበራችሁ በየ አለም ዳርቻ የምትገኙ ሙስሊም እህት ወንድሞቼ በያላችሁበት ለእናንተ ሰላም እና ደስታን አብዝቼ በመመኘት

አንድ ከአላህ ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ አኼራ ላይም ትልቅ ምንዳን የሚያስገኝ ምንዳው ከዘመን ዘመን የማይቋረጥ የአላህ ሱብሀነሁ ተአላ ቤት መስጅድን ለመገንባት በጋራ እንተባበር እላለሁ

ይህን መስጅድ ለመስራት ከተጀመረ 5ት አመትን ያስቆጠረ እስካሁኗ ሰአትም ድረስ ግን መጨረስ አልቻልንም

እናም ውድ እና የተከበራችሁ እህት ወንድሞቼ ተባብረን ከሰራን እንኳን አንድ መስጅድ መስራት አይደለም ብዙም እንሰራለን ሁላችሁም ከጎናችን ሁኑ!

ዛሬ ለዚህ መስጅድ አውጥተን ነገም አላህ ለኔ ብላችሁ እስኪ ምን ሰራችሁ በሰጠኅችሁ ገንዘብ ሲለን ይሄው ጌታዬ ይሄን መስጅድ ገብቻለሁ ብለን በኮፊደንስ የምንመልስ ሰዎች እንድንሆን በየትኛውም አለም ያላችሁ እህት ወንድሞች እጃችሁን ዘርጉልን ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!
እኛ የሸዋሮቢት እና አካባቢዋ ነዋሪዎች ስንሆን ጥሪው ግን በሁሉም አለም ያሉ ሙስሊም እህት፣ ወንድሞች፣እናት ፣አባቶችን ፣ በሙሉ ይመለከታል ።ኢንሻአላህ አብሮነታችሁን እንደምታሳዩን ተስፋ እናደርጋለን።
ስለ መስጅዱ ያለውን ጥቅል መረጃ ደውላችሁ ማረጋገጥ ለምትፈልጉ
የመስጅዱ ዋና ኮሚቴ ቁጥር
ሁሴን አሊ
+25 19 13 89 27 00
አዬ መሀመድ
+25 19 13 21 78 85
ማህሙድ ሙሀመድ
+25 19 11 97 69 04
በነዚህ ቁጥሮች መደወል እና ማረጋገጥ ትችላላችሁ
መነየት ለምትፈልጉ እህት ወንድሞች

ወደ ኢትዮጵያ መላክ ለምትፈልጉ
የመስጅዱ አካውንት ቁጥር
Account no,32 25 98 71 Bank of Abyssinia
ብላችሁ ማስተላለፍ ትችላላችሁ
ወጀዛኩሙሏሁ ኸይረን ወባረከላሁ ፊኩም
ወሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካትሁFollow this link to join my WhatsApp group: https://chat.whatsapp.com/F1PWyyCxDENBvCEQQU6Vp0
1.2K views19:18
Open / Comment
2022-02-14 14:47:46
አሏሁ አክበር በፓኪስታን በፑንጃብ ግዛት ውስጥ ቅዳሜ ዕለት ቁርኣን ሲያቃጥል የተገኘ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ውስጥ ቢገባም በአከባቢው የነበሩ ሰዎች ፖሊሶቹን ሳይቀር ከበው ልጁን ነጥቀው ደብድበው ገድለውታል።

በፓኪስታናውያን ዘንድ እስልምናን የሚሳደብ ማንኛውም ግለሰብ የሞት ፍርድ ይጠብቀዋል


አስሐቡል የሚን Page
http://t.me/AshaBuleyamine
1.1K viewsedited  11:47
Open / Comment
2022-02-13 21:08:38
ለማስታዎስ ያክል ከነገ እስከ ረቡዕ አያሙል ቢድ ናቸው።
ሰኞ 13
ማክሰኞ 14
ረቡዕ 15
ሐሙስን ጨምሮ 4ቱ ቀን የሱና ፆም ናቸው ። ፆም በላን ይመክታል እንፁም ወደ ጌታችን እንመለስ በዱዓእ እንበርታ ።
http://t.me/AshaBuleyamine
685 viewsedited  18:08
Open / Comment
2022-02-13 17:08:43
610 views14:08
Open / Comment
2022-02-13 17:08:37 https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q

በጹሑፍ ይቀርባል ¶
https://t.me/AshaBuleyamine/5125

ሠለምቴ ከሆኑ ጆይን ብለው የፕሮግራሙ እንግዳ ይሁኑ
https://t.me/Selmeta

አስተያየት ለመስጠት
http://t.me//Ashabulyeminbot

ለበለጠ መረጃ
https://t.me/Quran_is_life_Sari_A
539 views14:08
Open / Comment
2022-02-13 17:08:37 ሠለምቴው አብዲሳ ክፍል ሁለት.........።

ቢስሚላህ አልሀምዱሊላህ
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ። የአስሐቡል የሚን ቤተሰቦች ።

ዛሬ ኢንሻ አሏህ ከባለፈው የቀጠለ እነዴት ሰለምኩኝ የሚለውን ታሪኬን ልቀጥል እወዳለው በባለፈው ክፍል ወርቃማ ብዬ መግለፅ የማልችለው ስጦታ ከአሏሀ ተበረከተልኝ ብዬ ካቆምኩበት ኢንሻ አሏህ በአሏህ ውዴታ ልቀጥል እሻለው(ፈልጋለው) ሸሀዳ ከያዝኩ በኃላ በድብቅ(ቤተሰቦቼ ሳይሰሙ) ለሶላት ሚያስፈልገኝን
ጠሃር,ፋቲሃ,አተሂያቱ,አጫጭር የቁርአን አነቀፆችን,እንዴት እንደ ሚሰገድ ብቻ ምን አለፋችሁ ለሶላት የሚያስፈልገኝን ሁሉንም ካሟላው በኃላ በድብቅ(ቤተሰቦቼ ሳይሰሙ) ሶላቴን እየሰገድኩ ቀናቶች ባለፉ ቁጥር መስለሜን የሠሙ ሙስሊም ወንድሞቼ አንዳነዶቹ ማሻ አሏህ ሌሎቹ ደሞ አይዞህ በርታ እያሉኝ የተከበረው ወር ረመዷን መጣ! እድሜዬ 16 ለቤተሰቤ የመጀመሪያ ቤተሰቦቼን የምፈራ እነሱም በጣም የሚወዱኝ መሆናቸው ረመዷንን ለመፆም ድፍረት አሳጣኝ..........

አንድ ረመዷን ብቻ አይደለም ሌላ ሁለት ተጨማሪ ረመዷኖች መፆም አልቻልኩም። ግን የአሏህ እዝነት አያልቅምና 2013እ.ኢ.አ ሸዐባን ወር ውስጥ ጁሙአ ልሰግድ መስጂድ ስገባ እናቴ አይታኝ አባቴን ደውላ ጠርታው ከመስጂድ ኹጥባ እስኪያልቅ ድረስ ጠብቀው ከሶላት በኃላ ከመስጂድ ስወጣ እናቴ እና አባቴ በሩቁ ከፊትለፊቴ ሲመጡብኝ ተመለከትኩ ሳያዩኝ ቶሎ ብዬ ወደሆነ ቤት ስር እጥፍ ብዬ ተደበኩኝ ከዛ አጎንብሼ ያአሏህ ነስረኝ ብዬ ረህማኑን ለመንኩት ከዛ ቀና ስል እናቴ ፊትለፊቴ ቆማ እያለቀሰች "እኔን ላንተ ብዬ ያረጀውትን እናትክን ትሸጣለክ" አለቺኝ

አሏሁ አክበር መሬት ተቀዳ ብትውጠኝ ምኞቴ ነበር ከዛ እናቴ "ና አሁን ዝም በልና ከፊቴ ቀድመህ ሂድ አለቺኝ" እኔ ምንም እንዳልገባኝ ሆኜ ምነ ሆነሽ ነው እማ አልኳት አሷም ዝም በልና ና ወደቤት ሂድ አለቺኝ እኔም እምቢ አልኳት ከዛ እሷ ጥላኝ ሄደች ኡፍ ብዬ እነደተነፈስኩ በጣም ምፈራው አባቴ በሌላ መንገድ ዞሮ ሊይዘኝ ከፊትለፊቴ ከች ብሎ ናቅደም ሲለኝ ወላሂ አቅም አነሰኝ በድንጋይ አንዴ ተረከዜን ድብን አርጎ መታኝ ከዛ በጭንቅላቴ ውስጥ በቃ አሁን በአሏህ ልከፍር ነው ብዬ በድንጋጤ አያሰላሰልኩ ከፊቱ ቀድሜ ወደ ቤታችን አመራው ከመስጂድ አብረውኝ የወጡ ጓደኞቼ ግማሾቹ ከኃላ እየተከተሉ ግማሾቹ የአባቴን እጅ እንዳይመታኝ እየያዙ ሊያስጥሉኝ ቢሞክሩም አልቻሉም።

እናቴ ከኃላችን እየተከተለች አባቴ እኔን እየገፈተረኝ ወደ ቤት አቀናን! እቤት እንደደረስን አባቴ ግቢአችን ውስጥ የበቀለ ሸንበቆ ከነ ስሩ ነቅሎ እቤት አስገብቶኝ ይገርፈኝ ጀመር ሸንበቆውን እኔ ላይ ስብርብር ሲያደረግ አክስቴ (የእናቴ እህት) ቤት ውስጥ ነበረች መሀላችን ገብታ ትገላግል ጀመረች መግቢያ የጠፋኝ እኔ ደሞ አሁን ሰልሚአለው ካልኳቸው ሲህር (ድግምት) አድርገውብኝ ያከፈሩኛል ብዬ ስለፈራው መሸምጠጥ(መካድ) ጀመርኩ አባቴ ሸንበቆው እጁን ቆርጦ ስላደማው ደሙን ሊጠርግ ወጣ ሲል እናቴ ከውጪ እያለቀሰች ገባች ከዛ እሷ"ምነው ፈጣሪዬ ምን በድዬህ ነው ለጄን ምታሰልመው" ብላ ስታለቅስ እኔ ደሞ ማደርገው ስለጠፋኝ ኧረ አልሰለምኩም ብዬ እሟገታት ጀመር እሷም "ከመስጂድ ስትወጣ አይቼሃለው" እኔም "እኔ አይደለሁም" አልኳት ይሄን ሲሰማ ደሙን ሊጠርግ የወጣው አባቴ በንዴት "ዝም አትልም አሁን አፍህን ያዝ" እያለ እኛ አካባቢ (ሐረርጌ) ሜንጫ የሚባል የስለት መሣሪያ አለ አሱን አምጥቶ ሊመታኝ መኝታ ቤት ሲገባ
እኔ ይሄን አጋጣሚ ተጠቅሜ ሁለት ጫማዬን በእጄ ይዤ ፈረጠጥኩ ከዛ የሰፈራችን አንድ ሙስሊም ባለሀብት ቤት ገባው ቤተሰቦቼም ተከትለውኝ መጡ ከዛ በድንገት የት እንደገባው አጡኝ።

ከዛ በኃላ እዛው ቤት እያለው ሙደወር ለበስኩ ኢማማ ጭንቅላቴ ላይ ጣል አድርጌ ባጃጅ መጥቶ በር ላይ ቆመ ገባው ከዛ ሰፈር ወጥቼ ሊገምቱት የማይችሉት ሰፈር ሄድኩ አንድ ወንድማችን ቤት አረፍኩ።

ቤተሰቦቼ ደሞ ሰፈሩን ቀውጢ አደረጉት። ወዲህ ነው ነገሩ አባቴ ያለውን እውቅናና ገንዘብ ተጠቅሞ ሴራ ይሸርብ ጀመር በዛን ወቅት ወሎ ላይ ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል ግጭት ተፈጥሮ ነበር
የኔን መስለም ከወሎው ጉዳይ ጋር አያይዞ ሴራ ጠነሰሰ የምን ሴራ አትሉኝም "

ክርስቲያኑን ልጄን መስጂድ ወስደው ገድለውብኝ አንድ ክርስቲያን መስጂዱ ውስጥ ተገደለ ብለው ሙስሊም እና ክርስቲያኑን ሊያጋጩት ነው" ብሎ ለመንግስት አካል አሳውቆ ሰፈሩን በፖሊስ በሚሊሻ በልዩ ሀይል አጨናነቀው ከዛ ጓደኞቼን ልጄ የት እንዳለ ካል ነገራቹኝ አሳስረቹዋለው ብሎ ያስፈራራቸው ጀመር ከዛ ጓደኞቼ ደውለው ነገሩን አሳወቁኝ እኔም ነገሩ ስሰማ ወላሂ ምገባበት ነው የጠፋኝ ግን ከአሏህ ወዴትም አየሸሽም እና አሏህ ሆይ አደራ አታክፍረኝ ብዬ አልቅሼ ምንም የማይሳነውን ከአርሽ በላይ ያለውን ራህማኑን ለመንኩት ከዛ በሰው ስልክ ለአባቴ ደውዬ እኔ በእራሴ ፍላጎት ወድጄ እና ፈቅጄ እንደሰለምኩ ።

አስረዳሁት እሱ ግን ሊሰማኝ ፍቃደኛ አልነበረም እስከ አስራ ሁለት ሰዓት ካልተመለስክ ማደርገውን አውቃለው እንደውም ከፖሊስ ጋር አውራ ብሎኝ ስልኩን ለፖሊሱ ሰጠው ፖሊሱም የውሸት ዲሞክራሲውን እየነዛ "የፈለከውን እምነት መከተል መብትክ ነው" ብሎ ይሸብበኝ ጀመር ግን በድንገት ስልኩ ተቋረጠ ካርድ ጨርሶ ከዛ ልክ ከምሽቱ 12:00 ሲሆን አባቴ የሰፈሩን ቤት በጠቅላላ በፖሊስ ያስፈትሽ ጀመር ግን ምንም ማግኘት አልቻሉም እኔ ከዛ ሰፈር ጊዜ ሳላባክን እንደወጣው አላወቁም ከዛ ሌሊቱን ሙሉ ሲፈትሹ አደሩ የከተማችን ከንቲባ እንኳን አለቀረም በተጨማሪም አባቴ ለምዕራብ ሐረርጌ ዞን የኦርቶዶክስ እምነት አባቶች ደውሎ ተፅዕኖ ለመፍጠር ዘዴ አወጣ ግን አሏህ ከነሱ የበለጠ ዘዴ አውጥቶ እንደገና ሴራቸውን አከሸፈው........

ታሪኩ ብዙ ነው አላርዝምባቹ ከዛ በሚቀጥለው ቀን ልጄን ወሰዱብኝ ብሎ ክስ ሊመሠርት ወደ ሐረርጌ ዞን ፍርድ እየሄደ ሳለ የሰፈራችን ሰዎች እኔ አመጣዋለው ክስ ብትመሠርትም ምንም ማድረግ አትችልም ብለውት አረጋግተውት እኔ ያለሁበት አንድ ታማኝ ሰው ተላከ ከዛ ወደ ቀበሌ ፅ/ቤት ወሰዱኝ ከዛ እናቴ አባቴ አጎቴ የአክስቴ ልጅ ተሰብስበው መጡ እናቴ እና አባቴ ፊትለፊቴ ተቀመጡ እንዴት እንደሰለምኩ አስረዳዋቸው ይሄን ሲሰማ አባቴ የተናገረው ነገር ቢኖር እኔ ከዚህ በኃላ ልጄ አይደለህም ከኔ ምንም አትጠብቅ ወይም ደሞ ከእምነትህ ተመለስ አለኝ የኔ ምላሽ ግን እሱ እንደጠበቀው ቀላል አልሆነለትም የሰሃቦችን ልብ የሚነካ ታሪክ ሰምቼ ስለነበር እኔም እነዲህ አልኩት ከእምነቴ ከምመለስ የአንተ አባትነት ይቅርብኝ ከአንተ ምንም አልፈልግም ብዬ ፈረምኩለት እሱም አንተ የደረስክበት አልደርስም ብሎ ፈረመ ነገሩ እዚህ ላይ አበቃ አሏህ በእዝነቱ ነሰረኝ ከዛ ቤተሰቦቼ ያለሁበት ድረስ ሽማግሌ ልከው ወደ ቤት ተመለሼ የዘንድሮውን የመጀመሪያ ፆሜን 2013(1442) ረመዷን እቤተሰቦቼ ቤት ፆምኩኝ አል-ሀመዱ-ሊላህ! ታሪኬ እዚህ ላይ አበቃ..........

.በቅርብ ቀን በአስሐቡል የሚን ፕሮግራም ላይ በድምጽ የምቀርብ ይሆናል ። በዱአ አስታውሱኝ ወሠላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ።

የሠለምቴዎችን ታሪክ ለመከታተል ይወዳጁን





AS_HABULE YAMlNE TUBE
541 views14:08
Open / Comment
2022-02-13 01:00:57 https://t.me/joinchat/m8TRRsRrLj00MDlh

https://t.me/FezkuruniAzkurkum

ሳውዲ የኢትዮጵያ ሙስሊም ስደተኞችን አጉራ ማሰሯ የሚታወቅ ነው። ለዚህም ምክንያት እየተባለ የሚነገረው ወንጀል መስራታቸው ነው ቢባልም ብዙ ንፁሀን ሙስሊሞች ታፍሰው የታሰሩበት ወንጀል 'የትውልድ ሀገራቸው ኢትዮጵያ መሆኑ' ብቻ ነው። እነዚህ ሙስሊሞች ላይ ብዙ ግፍ እና መከራ ደርሶባቸዋል አሁንም እየደረሰባቸው ነው። እንደውም ይህ መከራ እርጉዝ ሴቶችን፣ ገና የወለዱ ሴቶችን፣ እንዲሁም ህፃናትን ሳይቀር ያካተተ ነበር። እየተሰቃዩ ያሉት ሙስሊሞች ወንጀላቸው የሳውዲ ዜጋ አለመሆናቸው ብቻ ነው። ይህ እውነታ እየታወቀ አሁንም ድረስ ለሳውዲ መንግስት ጠበቃ የሚቆሙ እና መሪወቾን የሙስሊም መሪ አድርገው የሚመለከቱ ሰወች በእርግጥም በትልቅ ጥመት ውስጥ ናቸው።  
284 views22:00
Open / Comment
2022-02-12 19:23:43
551 views16:23
Open / Comment