Get Mystery Box with random crypto!

AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር

Logo of telegram channel ashabuleyamine — AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር A
Logo of telegram channel ashabuleyamine — AS-HABULE YEMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር
Channel address: @ashabuleyamine
Categories: Uncategorized
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 7.32K
Description from channel

https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q
Telegram _Join
http://t.me/AshaBuleyamine
Twitter
https://twitter.com/AshabuleYamlne?s=09
Facebook page
https://www.facebook.com/Ashabuleyamine/
Website
http://ashabulyemin70.blogspot.com

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


The latest Messages 11

2022-02-12 19:23:37 ቢስሚላህ
ወደ እስልምና የመጣው ወንድማችሁ ነኝ ። ታሪኬ ይጠቅማል ብዬ ስላሰብኩኝ ነው በእንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም ላካፍላችሁ የፈለኩት ።

እስልምና መርጦኛል አልሃምዱሊላህ

ስሜ አብዲሳ እምሩ ይባላል የምኖረው በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ(አሰበ ተፈሪ) ሲሆን በአሏህ እዝነት ታሪኬን ላካፍላችሁ ወደጃለው አሏህ በራህመቱ በ2010 የኦርቶዶክስ ፆም ውስጥ ነበር የሰለምኩት(ከክህደት አለም የወጣሁት) ነገሩ ወዲህ ነው ስምንተኛ ክፍል እስክደርስ ድረስ የኖርኩት ካፊሮች (ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች) የሚበዙበት ሰፈር ነው ግን ልክ 2008 አካባቢ ስምንተኛ ክፍል ሳለው ሙስሊሞች ሚበዙበት ሰፈር 90% የሚሆኑት የሰፈሩ ነዋሪዎች ሙስሊም የሆኑ ሰፈር ገባን ሁለት አመት እዛ ከኖርን በኃላ ከሰፈሩ ሰው እየተላመድን ስንመጣ እኔም ከሙስሊም ልጆች ጋር ጓደኝነት ጀመርኩ ይሄን ጊዜ ነው እንግዲ የሂዳያ ስጦታዬን ለማግኘት ጉዞ የጀመርኩት።

ለጥናት ከሙስሊም ልጆች ጋር በምንገናኝበት ጊዜ ስለእምነት Discuss እናደርግ ነበር ።አንዳንዴም የከፋ ሙግት አደርግ ነበር! ከሙስሊም ጓደኞቼ ሀዲሶችን እሰማ ነበር ብዙ ጊዜ የእየሱስ ክርስቶስ (ነቢ ኢሳ) አሌይሂ ሰላም አልሞተም አልተሰቀለም የምትለዋን ነገር ስሰማ በጣም እናደድ ነበር። አንዳንድ ቀን ለብቻዬን ቁጭ ብዬ ልስለም አልስለም ብዬ ከአእምሮዬ ጋር ግጥሚያ ጀመርኩ

........."አሁን ልስለም ብል ቤተሰቦቼን ትቼ ነው ምሰልመው አይ ይቅርብኝ እነሱን ትቼ ከምሰልም ይቅርብኝ አይ" ብዬ ከአእምሮዬ ጋር ከባድ ጦርነት ገጥም ነበር ግን ከእለታት አንድ ቀን የህይወቴ turning point (ህይወቴ የተለወጠበት) ቀን ላይ ደረስኩ ትዝ ይለኛልእኔ እና ሁለት የሙስሊም ጓደኞቼ ቁጭ ብለን ባለንበት ምላሴ ከአእምሮዬ ጋር ሳይማከር በድንገት ሙስሊም መሆን ፈልጋለው የሚል ቃል ተናገረ!

ከዛ እነሱም የሰሙትን ማመን አቅቷቸው እ እ እያሉ በግርምት ያዩኝ ጀመር እኔም በድጋሚ አው ሙስሊም ለመሆን ምን ማድረግ አለብኝ ብዬ ጠየኳቸው እነሱም ምንም ማድረግ አይጠበቅብህም ሸሀዳ ብቻ ማለት ነው ሚያስፈልግህ ። ከአንገቴ ላይ ካንጠለጠልኩት
የሽርክ ገመድ እና መስቀል በሸሀዳ ቃል ድኛለው (መሬት ላይ ያለ ነገር በሙሉ የሷን ያህል መመዘን የማይችለውን ቃል) አልኩኝ በአሏህ እዝነት አልሀምዱሊላህ ወደ ተወለድኩበት እምነት ወደ እስልምና ተመለስኩ ወርቃማ ብዬ መግለፅ ማልችለው ስጦታ ከአሏህ ተበረከተልኝ.............

. ኢንሻ አሏህ ክፍል ሁለት ይቀጥላል አብዲሳ ነኝ ሠለምቴው ። ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ

የሠለምቴዎችን ታሪክ ለመከታተል ይወዳጁን
የሠለምቴዎችን ልዩ የእንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም ታሪኳቸውን ለማድመጥ :-





AS_HABULE YAMlNE TUBE

https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q

በጹሑፍ ይቀርባል ¶
https://t.me/AshaBuleyamine/5125

ሠለምቴ ከሆኑ ጆይን ብለው የፕሮግራሙ እንግዳ ይሁኑ
https://t.me/Selmeta

አስተያየት ለመስጠት
http://t.me//Ashabulyeminbot

ለበለጠ መረጃ
https://t.me/Quran_is_life_Sari_A
563 views16:23
Open / Comment
2022-02-11 21:28:25 እንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም
የሰለምቴዋ ማህሌት


891 views18:28
Open / Comment
2022-02-11 19:06:25

926 viewsedited  16:06
Open / Comment
2022-02-03 19:00:45 ከሰለምቴዋ ማህሌት እሥልምናን ስትቀበይ ምን ተሰማሽ ስትባል እንደ ገና የተወለድኩኝ ያህል ተሰምቶኛል ብላለች..!


እሥልምናን ስለተቀበልኩኝ ብቻ የትም አውጥተው ጣሉኝ ልጅ ነኝ ከሰው ሃገር የማውቀው ሰው የለም። ሊገሉኝም ሞክረው ነበር ለሶስት ቀን ጎዳና ላይ ቆይቻለው ።

ከሃገር ኢትዮጵያ የወጣሁት ገና የሁለት አመት ልጅ እያለሁኝ ነው ።

እናቴ የሞተችብኝም ህጻን ሆኜ ነው ። ታዲያ ያሳደገችኝ አክስቴ እሥልምናን ስቀበል በማላውቀው ሃገር አውጥታ ጣለችኝ ። ባሏም የአይሁዳውያን እምነት ተከታይ ነውና ከእሥልምና ባለው ጥላቻ የተነሳ ጥቃት አደረሰብኝ ። ወደ እናት ሃገር ኢትዮጵያ በአስሓቡል የሚን ጀመዓዎች እርዳታ ልገባ ችያለው ከወደኩበት ከሰው ሃገር አንስተውኛል ። እናትም አባትም እህትም ወንድምም የለኝም በቃ አንድ ነኝ ማንም የለኝም። አሏህ የወደደውን ይፈትናል ይባላል አይደል .? እኔም ፈተናዎች ቢደራረቡብኝም ግን እሥልምናዬ ሰላም ሰጥቶኝ ያጽናናኛል ።

ማህሌት በቅርብ ቀን በአስሓቡል የሚን ሥር




ቴሌግራም .......
https://t.me/+RXYpviFTL70OQdu2
776 views16:00
Open / Comment
2022-02-03 15:51:52

871 views12:51
Open / Comment
2022-02-01 20:51:07
1.2K views17:51
Open / Comment
2022-02-01 20:51:04 በፊት የካቶሊክ እምነት ተከታይ ነበርኩኝ ስሜም ምህረት ይባላል ። ምህረት በእንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም ።

ኢሥልምናን እና የክርስትናን ምንነት ለማወቅ የቻልኩት በድንገት በማላውቀው ሰው ከንጽጽር ግሩፕ ላይ አድ በተደረኩበት ታይም ነው። ንጽጽር ግሩፑም የኡስታዝ ሙሐመድ ኸድር ዒሳ ነበር ።

ውይይቶችን እያደመጥኩኝ እያደመጥኩኝ ሳለ
ኢየሱስ አምላክ አለመሆኑን ሙሥሊሞች ሲያወሩ በጣም ተናደድኩኝ ። በውስጥ እየገባሁኝ ኡስታዝን እሳደባለው ልጆችን እሳደባለው። ለምን ብቻ ኢየሱስ አምላክ አይደለም አላችሁ ብዬ

እነርሱም የሆነ ጥቅስ ሰጡኝ ከባይብል ማርቆስ ፍእራፍ 12 29 በሰጡኝ ጥቅስ በጣም ተገረምኩኝ እና ማሰብ ጀመርኩ ። ባይብልንም ገልጬ አየሁኝ ጌታ አምላካችን ነው እንጅ ያለው ጌታ አምላካችሁ አላለም ።እዚህ ጋር ኢየሱስ የእኛም የእርሱም አንድ አምላክ እንዳለ በመጥቀስ እርሱም አምላክ እንዳልሆነ ያሳያል ።

ለሁለት ዓመት ያህል በሃይማኖት ንጽጽር ላይ ዘገየሁ። በመካከል ግን ስለ እምነት ያለኝ ትኩረት እና እሳቤዬ ቀጠለ ። ካቶሊክንም እሥልምናንም ማየት እና ማነጻጻር እና ማጣራት ጀመርኩ ።

እሥልምናን ቶሎ አልተቀበልኩም ነገር ግን ባለሁበት እምነት ላይ ሆኜ ብጸልይም ምንም ብል ውስጤ ደስተኛ ሆኖ እየተቀበለኝ አልነበረም ። ቀስ በቀስ ከካቶሊክ ርቄ ወደ እሥልምና ቀረብኩኝ ። ከባይብል ላይ ያሉትንም ጥቅሶች እያነበብኩኝ ማገናዘብ ያዝኩኝ ። ኢየሱስም ወደ ተራራ ወጥቶ እንደ ፀለየ እዚያው ባይብል ላይ ይናገራል።
ሉቃስ 6- 12 በእነዚያም ወራቶች ሊፀልይ ዘንድ ወደ ተራራ ወጣ ሌሊቱን ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ሲፀልይ አደረ ይላል።

ይህንን ሳነብ አምላክ እንዴት ለሌላ አምላክ ይፀልያል ? የሚለው ጥያቄ ፈጠረብኝ ።እስከዛሬ የት ነኝ ብዬ እራሴን ጠየኩኝ።
ዩሐንስ 7- 16 ትምህርቴ ከላከኝ ነው እንጅ ከእኔ አይደለም ይላል ። የላከኝ ሲል ኢየሱስን የተላከ እና የላከው ደግሞ ሌላ አካል እንዳለ እየነገረን ነው ።ይህ የሚያሳየው ነቢይ መሆኑንም ነው ።

ዩሐንስ 14-24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም የምትሰሙት ቃል የላከኝ አብ ነው እንጅ የእኔ አይደለም ይላል ።
ቆም ብለን ማሰብ ያለብን ይህ ሁሉ ጥቅስ ባይብል ውስጥ ነው ያለው ።ኢየሱስ አምላክ እንዳለው እና ከአምላኩ ዘንድ የተላከ ነቢይ ፍጹም ሰው መሆኑንም እየነገረን ነው ። ታዲያ የእኛ የሙጢኝ ብለን አምላክ ነው የምንለው በምን መረጃ ነው ..!? መጽሐፍ ቅዱስ ቀጥታ የሚነግረንን እኛ ግን በፈለገን በግራም በቀኝም እያዞርን ነው የምንጓዘው ።

መምህሮቻችን እራሱ አይ ኢየሱስ እራሱን አምላክ ነኝ ብሎ መግለጽ ስለማይፈልግ ነው ብለው የሚነግሩን ጊዜም ነበር ። ግን ይገርማል አምላክ ከሆነ እንዴት በማንነቱ ያፍራል ? እንዴትስ የእኛም የእርሱም ፈጣሪ ሌላ አምላክ እንዳለ ይናገራል ? ቆም ብለን ማሰብ ያስፈልጋል ።

ሌላው ቅዱስ ቁርባን ነው። ቅዱስ ቁርባን የሚዘጋጀው ከስንዴ ነው ።ስንዴው ይፈጫል ይሞካል ይጋገራል ። ከተጋገረ በኋላ የራሱ የሆነ ቅርጽ ማውጫ አለው በዚያ ይቆረጣል ። ይህንን እኔም አዘጋጅ ነበር ።

ግን ይህ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እና ሥጋ የሚባለው ከኸምር ከወይን ጠጅ ነው የሚዘጋጀው ።
የተዘጋጀው ስንዴ ሥጋው ነው ...!
ከኸምር ከወይን ጠጅ የሚዘጋጀው ደግሞ ደሙ ነው ይባላል ።

እንዴት ነው ይሄስ ነገር .? በእምነቴ አለም ውስጥ እያለሁኝ ምንም አይመስለኝም ነበር ግን ጥናት እና ምርምር ስጀምር እንዴት ነው የአምላክ ደም እና ሥጋ ሊሆንስ የሚችለው ብዬ ውስጤን በጥያቄ ማጨናነቅ ጀመርኩኝ ።

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በኤፌሶን 5- 18 ላይ መንፈስ ይሙላባችሁ እንጅ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና ይላል ። እዚህ ጋር በወይን ጠጅ አትስከሩ እያለ እነርሱ ደግሞ በግልባጭ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው ብለው ኸምርን እየነከሩ ይሰጡናል ።

እሥልምናን ከተቀበልኩኝ በኃላ አንድ ቄስ ጋር በመደወል አባ ኤፎሶን 5- 18 ላይ እንዲህ ይላል ብዬ ነገርኳቸው ። እንዴትስ መጽሐፉ ይህንን እያለ እናንተ ግን ቁርባንን የምታስፈጽሙን በዚህ ነው ብዬ አልኳቸው ። እነርሱም አትስከሩ ነው እንጅ ያለው መጠጣቱ ይቻላል ብለው መልስ ስጡኝ ሱብሃነሏህ። በጣም ነው የገረመኝ ። ስለታቦትም ጠየኳቸው በጎግል ሰርች አድርገሽ እይውና አንብቢ ይህንን ለመመስ ጊዜ የለኝም አሉኝ ።

ይሄስ እንዴት ነው ? ቆም ብለን እናስብ !

እኔ ግን ኢትዮ ውስጥ አምልኮ ስለሚሰጡት 44 ታቦቶች መልስ ፈልጌ ነበር ።
አልሃምዱሊሏህ የእሥልምናን መምህሮች ሳላደንቃቸው አላልፍም ። አንድን ነገር ስንጠይቅ ወዲያውኑ መልስ ይሰጡናል ።

እኔ እውነትን አግችኜ አምላኬ መርቶኝ ትክክለኛውን መንገድ አግኝቻለው። አለማወቅ ኃጢኣት አይደለም ነገር ግን እያወቅንም ሆነ ላለማወቅ ችላ ማለታችን ዋጋ ያስከፍላል ።እምነት ማለት የማንኛውም ሰው የግሉ የህይወት ጎዳና ነውና አንብቡ እወቁ ያላችሁበትንም እምነት መርምሩ እላለሁኝ። ምህረት ሠለምቴዋ ጸሐፊ ሳራ ሰለምቴዋ ።

የሠለምቴዎችን ልዩ የእንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም ታሪኳቸውን ለማድመጥ :-





AS_HABULE YAMlNE TUBE
https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q

በጹሑፍ ይቀርባል ¶
https://t.me/AshaBuleyamine/5125

ሠለምቴ ከሆኑ ጆይን ብለው የፕሮግራሙ እንግዳ ይሁኑ
https://t.me/Selmeta

አስተያየት ለመስጠት
http://t.me//Ashabulyeminbot

ለበለጠ መረጃ
https://t.me/Quran_is_life_Sari_A
1.2K viewsedited  17:51
Open / Comment
2022-01-31 11:46:13 አስ-ሓቡል የሚን!

አስሓቡል የሚን ዘርፈ-ብዙ እና መጠነ ሰፊ መርሓ-ግብር የያዘ ተቋም ነው። በአሁን ሰዓት በገጠሩ ክፍል ሚሽነሪዎች በጥቅማ ጥቅም የሚደልሉበትን ቦታ እግር በእግር እየተከታተል ሙሥሊሙን የሚደጉም፣ መድረሳ በማቋቋም፣ ቁርኣን የሚያስቀራ፣ ሠለምቴዎችን በመሰብሰብ ታሪካቸውን በማቅረብ ለሠለምቴዎች በእርዳታ የሚደግፍ ሰዎችን ወደ ዲኑል ኢሥላም የሚጣራ ተቋም ነው። ይህንን ተቋም በንዋይ(በገንዘብ)፣ በአሳብ እና በጉልበት መደገፍ የምትፈልጉ ሊንክ በማስፈንጠር ተጭነው ይግቡ ወይም
ባሉበት ሆነው አስሓቡል የሚንን ጀመዓህ መደገፍ ይችላሉ

አባይ ባንክ 618741381 0591017

ዳሽን ባንክ -2928011755411

ንግድ ባንክ - 1000393327727

ቴሌግራም፦

https://t.me/joinchat/Th93dNNUa7fV1c79

ዋትስ-አፕ
https://chat.whatsapp.com/6O1nFgi4oKHLgB1fdY0Air

በጉልበት እና በሃሳብ ጊዜኣችሁን ሰታችሁ በመልካም ሥራ ላይ ለማገዝ የምትፈልጉ እህቶች ከታች ባለው አድራሻ ያግኙን ።
http://t.me/a_Bint እህት ኢማን
http://t.me/OBintMahmud እህት የትም-ወርቅ
https://t.me/Quran_is_life_Sari_A እህት ሳራ

ለበለጠ መረጃ
+971544106845
+966503917209
+251926142009
+966554225870
አስሓቡል የሚን የዑማው ብርሃን
1.4K views08:46
Open / Comment
2022-01-28 22:40:23 AS-HABULE YAMINE (የቀኝ ጓዶች) ማህደር pinned a photo
19:40
Open / Comment
2022-01-28 22:37:42 ወንድማችን ወደ ኢስላም የገባበት የምስክርነት ቃል
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር
አላህ ( ሱ.ወ )ፅናቱን ይስጥህ


وَقُلْ جَآءَ ٱلْحَقُّ وَزَهَقَ ٱلْبَٰطِلُ إِنَّ ٱلْبَٰطِلَ كَانَ زَهُوقًا

: በልም «እውነት መጣ ውሸትም ተወገደ፤ እነሆ ውሸት ተወጋጅ ነውና፡፡»(17:81)
368 views19:37
Open / Comment