Get Mystery Box with random crypto!

Blaze Movement

Logo of telegram channel blazemovement — Blaze Movement B
Logo of telegram channel blazemovement — Blaze Movement
Channel address: @blazemovement
Categories: Telegram , Religion
Language: English
Subscribers: 1.62K
Description from channel

Blaze Movement is an annual international youth movement. It gathers the youth from around the world for a one month program which is concluded by huge musical concert at you go church. @ab_hailu

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


The latest Messages 3

2022-03-13 15:24:24
Coming Sunday afternoonl local time 10:30 @beza church
774 viewsedited  12:24
Open / Comment
2022-03-10 23:30:01
714 views20:30
Open / Comment
2022-03-10 23:29:55
𝔽𝕣𝕚𝕕𝕒𝕪 ℕ𝕚𝕘𝕙𝕥


በእምነት | Bemnet
ዓርብ መጋቢት 02
11:30 (Local time)
ዩጎ ቸርች
𝕁𝕖𝕤𝕦𝕤 𝕀𝕤 𝕄𝕠𝕣𝕖 𝕋𝕙𝕒𝕟 𝔼𝕟𝕠𝕦𝕘𝕙!
604 viewsedited  20:29
Open / Comment
2022-02-17 17:58:55
𝔽𝕣𝕚𝕕𝕒𝕪 ℕ𝕚𝕘𝕙𝕥

ኤቢ | AB
ሚና | Mina
ዓርብ የካቲት 11
11:30 (Local time)
ዩጎ ቸርች
𝕁𝕖𝕤𝕦𝕤 𝕀𝕤 𝕄𝕠𝕣𝕖 𝕋𝕙𝕒𝕟 𝔼𝕟𝕠𝕦𝕘𝕙!
126 viewsedited  14:58
Open / Comment
2022-02-13 09:22:19 በተጨማሪም ጌታን ከተቀበልን በኃላ እንኳን በመንፈስ ሳንመራ ቀርተን ኃጢአት እንኳን ብንሰራ ከአብ ዘንድ ጠበቃ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳለን ቃሉ ስለሚል እኛም በዚህ ስንታመን በመስቀል ላይ አንዴ የተሰራልን ኃጢአትን ድል የማድረግ የመስቀሉ ስራ(ስሙ)(ኢየሱስ ክርስቶስ) ጠበቃ ሆኖ የዲያቢሎስን ክስ ድል እንደሚያደርግልን የሚገልጽ እና ያ የመስቀሉ የመማለድ ስራ በስሙ ስንጸልይ አሁንም ሕያው ሆኖ (ትኩስ ሆኖ) ለሰራነው ኃጢአት ዛሬም ስለሚማልድልንና ከየትኛውም ክስ ስለሚከራከርልንና ነጻ በማውጣት ከኃጢአታችን ስለሚያነጻንና ዲያቢሎስን ስለሚያሳፍረው ነው፡፡ በመሆኑም ደሙ ትኩስ አይደለም መማለዱ መስቀል ላይ ብቻ የቀረ እና ከትንሳኤ በኃላ አይሰራም ማለት የኪዳኑን ደም የመማለድ ስራ እንደማክፋፋት ነው። እንደ ቃሉም ያለቀና የተፈጸመ መስዋዕት ሲሆን የዘለአለም የማማለድ መስዋዕት ሆኖ በዘላለም መንፈስ የቀረበ ነው፡፡
ዕብ.9፡14
‹‹ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ስራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?››
በመሆኑም የመስቀሉ ስራ (የኢየሱስ ስም) አሁንም አይማልድም ብለው ኦርቶዶክሶች በማመናቸው በስሙ ውስጥ ያለውን የመማለድ ጉልበት እንዳይጠቀሙ በማድረግ በስሜ ለምኑ የሚለውን በመካድ የመስቀሉን መካከለኛነት አሁንም በስሙ እንደቀጠለ ባለመረዳት እንደማይሰራ በማሰብ በሌሎች ስም እንዲለምኑ አድርጓቸዋል፡፡ ይሄም የማስታረቅ አገልግሎት የሰጠንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ በመዘንጋት የማስታረቅ አገልግሎቱም የመስቀሉ ስራ(ስሙ) እንደሆነ ባለማስተዋል ሌላ የማስታረቅ አገልጋይ እና የማስታረቅ አገልግሎት(ስም) በመፈለግ ለመስቀሉ የማዳን ስራ ሌላ አማራጭ ይዘዋል፡፡ ቃሉ ያስተማረን ግን እግዚአብሔር ያዘጋጀልን የማስታረቅ አገልግሎት ለመዳንም ለሕይወትም የምንማጸነው በመስቀሉ ስራ (በስሙ) ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስም በዚህ መልኩ ለሚቀርብ ጸሎት ብቻ የይቅር ባይነት ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ የሚለመንበትን የመስቀሉን ስራ(ስሙን) በሌላ መተካት ደግሞ አምልኮ ነው፡፡


Copied from Seifu kiniso “Facebook “
29 views06:22
Open / Comment
2022-02-13 09:22:19 ቃሉ በአብ ቀኝ ከገባ በኃላ እንደማይለምንልን ቢነግረንም ነገር ግን አስቀድሞ የሚያዘን ነገር አለ፡፡ ‹‹በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤…›› ይላል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ ክፍል ቁጥር 24 ላይ ‹‹እስከአሁን በስሜ ምንም አልለመናችሁም ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ፡፡›› ይላል፡፡ እነዚህ ቃሎች እንደሚስረዱን በስሙ መለመን እንዳለብን ነው፡፡ በስሙ ደግሞ መለመን ማለት በመስቀሉ ስራ መለመን ማለት ነው፡፡ የሚያማልደውም የመቀስሉ ስራ(ስሙ) ነው፡፡ የመስቀሉ የመማለድ ስራ(ደሙ) በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ብቻ የሚሰራ ሳይሆን አሁንም ትኩስ ነው፡፡ ዘወትርም በአብ ቀኝ በሕይወት ስለሚኖር ደሙ ዛሬም ትኩስ ሆኖ የመስቀሉ ስራ(ስሙ) ዛሬም ይማልዳል፡፡ በስሙ ለምኑ የተባልነውም በመስቀሉ ስራ ታምነን እንድንለምን ነው፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ደግሞ በዚህ አለም ብቻ ሳይሆን ሊመጣ ባለው አለም ጭምር ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፋራ በቀኙ ሲያስቀምጠው ይሄ ስም የምንድንበት ስም እንዲሆን ነው፡፡ በመሆኑም በስሙ ስንፀልይ ስሙ መስቀል ላይ ከተሰራልን ስራ የተነሳ ከመኃላ ጋር የሊቀካህንነት ማዕረግ አለውና አዲስ ልመና ሆነ፣ መስዋዕት ሆነ፣ የሊቀካህንነት ስራ ሳያስፈልግ ስሙ ያድነናል፡፡ እንደፈቃዱ የሆነ ጸሎትም እንደ መኃላ ይፈጸማል፡፡ በሰማይም ተቀባይነት ያገኛል፡፡ በመሆኑም በመስቀሉ ስራ የሆነው ሊቀካህንነት ከመኃላ ጋር ዘላለማዊ እና ሌላ የክህነት ስራ የማያስፈልገው ሹመት ነው፡፡
ስለዚህ መስቀል ላይ በተሰራው ስራ የኢየሱስ ስም ወደ አብ የምንጸልይበት እና ስሙን ስንጠራ ይህ ስም መስቀል ላይ ስለማለደልን ከዚህ ስም የተነሳ አብ ይቀበለናል፡፡ ወይም አብ፣ወልዱ፣መንፈስ ቅዱስ ይቀበሉናል፡፡ ምክንያቱም በመስቀሉ የመማለድ ስራ አምነን በስሙ እየጸለይን ነውና! ሊዚህ ነው ቃሉ ዩሐ.14፤14 ‹‹ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ፡፡›› የሚለን፡፡ በስሙ አለመለመን ከመስቀሉ ሌላ የመማለጃ መንገድ አለ ብሎ እንደማሰብ ነውና እግዚአብሔር አይቀበለውም፡፡
በተጨማሪም በስሙ የተላከው መንፈስ ቅዱስ (ዩሐ.14፤26 አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ የተባለው) በሮሜ መጽሐፍ ላይ እንደተጻፈው፡-
(ሮሜ 8 )
26 እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤
27 ልብንም የሚመረምረው የመንፈስ አሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል፥ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ ቅዱሳን ይማልዳልና።
ይህ በስሙ የተላከው የትንሳኤው መንፈስ ከዚህ የመስቀል ስራ(የመማለድ ስራ)(ከስሙ) የተነሳ የመስቀሉን ስራ በእኛ ውስጥ ለመስራት እንድንጸልይ (መንፈስ ቅዱስ ካልረዳን እንዴት መጸላይ እንዳለብን ስለማናውቅ) በማድረግ በውስጣችን ሆኖ በመቃተት ለራሳችንም ህይወት ስለቅዱሳንም ይማልድልናል፡፡ ይህም በእግዚአብሔር ፊት አዲስ ልመናን ያቀርባል ማለት ሳይሆን በክርስቶስ የተፈጸመውን የመማለድ ስራ (የመስቀሉ ስራ) በእኛ ውስጥ በማመን ውጤት እንዲኖረው በፈቃዳችን ወደ እርሱ በመፀለይ በመስቀሉ ስራ እንድንታመን ለመንፈሳችን ድምጹን በማሰማት ነፍሳችን ወደ መስቀሉ ስራ ትኩር ብላ እንድትመለከት በማድረግ መልስ ከመስቀሉ ከተፈጸመው ድል ታስተውል ዘንድ ይቃትታል፡፡
እኔ አስከምረዳው የመስቀሉ ስራ እንዴት ይማልዳል ብሎ የሚጠይቅ ኦርቶዶክስ አማኝ ያለ አይመስለኝም፡፡ ሁሉም በመስቀል ላይ መማለዱን ያምናልና! አሁንም በዚህ ሰአት ስሙ (የመስቀሉ ስራ) ለሚመኩበት አይማልድም ልትሉ እንደማትችሉም እረዳለሁኝ፡፡ በመሆኑም ይማልዳል ስንል ስሙን (የመስቀሉን) ስራ እንጂ አሁንም ይለምናል ማለት እንዳልሆነ ልንረዳ ይገባል፡፡ በተጨማሪም እንደምታስቡት ኢየሱስ ስሙ (የመስቀሉ ስራ) ይማልዳል ስንል በመስቀል ላይ ከሰራው ስራ የተነሳ በአብ ቀኝ በመቀመጡ እንደመልከጸዴቅ ሹመት ለዘለአለም ሊቀካህን በመሆኑ እንደ ሹመት ከመኃላ ጋር (የቀድሞ ሊቀካህናት ልመናቸው ውድቆ ሆኖ እራሳቸውም ሊቀሰፉም ጭምር የሚችል ሲሆን የኢየሱስ ግን ከመኃላ ጋር ለዘላለም በስሙ ለሚለምን መልስ እንደሚቀበል ማረጋገጫ ነው፡፡) ስሙ ይማልዳል፡፡ ስለዚህ ይማልዳል ማለት በቃሉ በታዘዝነው መሰረት በስሙ መፀለይ ሲሆን ስሙ(የመስቀሉ ስራ) ሊቀካህኑ መስዋዕቱ ተቀባይነት አግኝቶ ለዘላለም አንዴ በፈጸመው የክህነት አገልግሎት እንደመልከጸዴቅ ሹመት ከመኃላ ጋር ይማልዳልናል፡፡
ቃሉ በ2 ቆሮ 5: 18 ላይ "ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ አለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቸውንም አይቆጥርባቸውም ነበር፤…" ይላል፡፡
በመሆኑም እንደቃሉ አስታራቂም እርሱ፣ የማስታረቅ አገልግሎት የሰጠን እርሱ፣ የምንታረቀው ከእርሱ፣ ይቅር የሚለንም እርሱ ነው፡፡ በመሆኑም መንገዱም እርሱ፣ ሕይወቱም እርሱ፣ የሚደረስበትም እውነት እርሱ ነው፡፡ ስለዚህ በስሙ (በመስቀሉ ስራ) እንለምናለን፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስም ይለመኑናል፡፡ ይህንን መርህ አፍርሰን በሰው ስም፣ በመለአክት ስም ብንለምን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ወጪ ሌላ ትምክህት ከኔ ይራቅ የተባለውን ረስተን አስታራቂው እግዚአብሔር፣ የማስታረቁ አገልግሎት የሰጠን እግዚአብሔር፣ የምንታረቀውም ከራሱ ከእግዚአብሔር ጋር መሆኑን ረስተን ሌላ አስታረቂን በማምጣት የማስታረቅ አገልግሎቱን (የመስቀሉን ስራውን) እንደመካድ ይቆጠራል፡፡ ቃሉም ሐዋ.4፤12 ላይ ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና፡፡›› በማለት ይደግፈናል፡፡ ከመስቀሉ ስራ(ከስሙ) ወጪ ሌላ ስም አለ ማለት የመስቀሉን መንገድነት (የማስታረቅ አገልግሎት) መካድ እና ለሰዎች ወደ አምላክ የሚቀርብ ልመናን በሌላ ስምም እንደሚቻል በማስተማር ከመስቀሉ ውጪ(ከስሙ ወጪ) ሌላ አማራጭም አለ ማለት ስህተት ማስተማር ነውና!
ኢየሱስ በመስቀል ለይ የማለደልን ስራ የዘላለም መማለድ ስራ እንደሆነ መካድ አያስፈልግም፡፡ አሁን እንኳን ከስሙ (አንድ ጊዜ መስቀል ከተሰራው ስራ) የተነሳ መንፈስ ቅዱስ ለእኛም ለቅዱሳንም በውስጣችን ሆኖ በመቃተት የመስቀሉን ስራ ሁልጊዜ ከልባችን እንዳይጠፋ ይማልድልናል፡፡ ይህንን የመንፈስ ቅዱስን የመስቀሉ ስራ(ስሙን) በውስጣችን የማጽናት ስራ አለመቀበል በስሙ የመጣውን እና ስሙን የሚያከብረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መካድ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም በስሙ በሆነው በመስቀሉ የመማለድ ስራ እንድንደገፍ የመስቀሉን የመማለድ ድምጽ በማሰማት ምልጃውን እንድንቀበል ያግዘናል፡፡ በመሆኑም በመስቀል ላይ የተሰራው የመማለዱ ስራ ለመዳን ብቻም ሳይሆን ሕይወታችን እርሱን መስሎ እንዲኖር ጭምር በመሆኑ መንፈስ ቅዱስም ይህንን ለማሳካት በመስቀሉ ስራ እንድንታመን እና የመስቀሉ ስራ በእኛ ሕይወት እንዲሰራ በስሙ (በሚማልደው) እንድንለምን በማድረግ ምልጃው በሕይወታችን እንዲገለጥ በውስጣችን ይቃትታል፡፡
21 views06:22
Open / Comment
2022-02-13 09:22:19 ለኦርቶዶክስ እና ለፕሮቴስታንት አማኞች
ኢየሱስ ክርስቶስ በየቀኑ ወደ አብ ቀኝ እየቀረበ ይለምንልን (ይማልድልን) ይሆን? በፍጹም!

ለኦርቶዶክስ እና ለፕሮቴስታንት አማኞች
ኢየሱስ ክርስቶስ በየቀኑ ወደ አብ ቀኝ እየቀረበ ይለምንልን (ይማልድልን) ይሆን? በፍጹም!

ኦርቶዶክሶች ፕሮቴስታንቶች ኢየሱስ ክርስቶስ ይማልዳል ሲሉ የሚያስቡት ከትንሳኤም በኃላ ወልድ በአብ ቀኝ ሆኖ ወደ አብ በየቀኑ ይለምናልናል (ይማልዳልናል) የሚለውን ነው፡፡ ከብዙ ኦርቶዶክሶች ጋር ባደረኩት ውይይት እንደተረዳሁት እኛ የምንለውን ባለማብራራታችን እንዳልገባቸው እና እኛም ፕሮቴስታንቶች አብዛኞቻችንን ያማልዳል ከማለት ውጪ ገልጠን መጽሐፍ ቅዱስ አረዳዱን ማስረዳት አለመቻላችን ትልቅ ክፍተትን ፈጥሯል፡፡
ኦርቶዶክሶች ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ራሱን በመሰዋት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የነበረውን የጠብ ግድግዳ ያፈረሰ መካከለኛ መሆኑን ያምናሉ፡፡ በምድር እያለ በመስቀል ላይ እንደማለደ ኢሳ 53፡12 ላይ እንዳለው ቃል መሰረት ‹‹…ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና ከአመፀኞችም ጋር ተቆጥሯልና እርሱ ግን የብዙዎችን ኃጢአት ተሸከመ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ፡፡›› በሚለው ቃል መሰረት በመስቀል ላይ መማለዱን ያምናሉ፡፡ በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ በመስቀል መስዋዕት በመሆን፤ መስዋዕት አቅራቢው ሊቀ-ካህናት እርሱ፤ መስዋዕቱም እርሱ፤ መስዋዕት አሳራጊውም እርሱ፤ መስዋዕቱን ተቀባዩም /ይቅር ባዩም/ እርሱ ራሱ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ይህም መስዋዕት አንድ ጊዜ ለዘላለም የቀረበ መሆኑን እና ፍጹም በመሆኑም እንደ ኦሪት ካህናት መስዋዕት አይደማይደገም፤ እንደማይከለስም ያምናሉ፡፡ ይሄ በእርግጥም ንጹህ ወንጌል ነው፡፡
በተጨማሪም ዩሐ.16፡26 ላይ ‹‹በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ እኔም ስለእናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም፤ እናንተ ስለወደዳችሁኝ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣሁ ስላመናችሁ አብ እርሱ እራሱ ይወዳችኃልና›› በሚለው ጥቅስ መሰረትም ወደ አብ ቀኝ ካረገ በኃላ ምንም አይነት ልመናን (ምልጃ) እንደማያቀርብ ጥቅሱ በግልጽ ይናገራልና በአብ ቀኝ ሆኖ ልመናን አያቀርብም በሚል አይማልድም በሚል ይደመድማሉ፡፡ እኛም በተመሳሳይ በአብ ቀኝ ከገባ በኃላ አዲስ ልመናን አያቀርብም ብለን ብናምንም አይማልድም ብለን ግን አንደመድምም፡፡ ምክንያቱም ዕብ.7፡25 ላይ ‹‹ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል፡፡›› የሚለውን ጥቅስ መሻር አንችልምና! ታዲያ ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው ስንል ምን ማለታችን ነው? በአብ ቀኝ ከገባ በኃላ አይለምንም እስከሚለው ከኦርቶዶክሶች ጋር ከተስማማን አሁንም በአብ ቀኝ ሰለእኛ ሊያማልድ በሕይወት ይኖራል ቃሉ ሲል እኛም ስንቀበል መረዳቱ እንዴት ነው የሚለው ቃሉ ብሏልና ሊፈታ እና ሊገባን ይገባል፡፡ አንደኛውን ቃል ለማጽናት ስንል ሌላኛውን ቃል አንሽረውምና!
አየሱስ ክርስቶስ በጎልጎታ በመስቀል ላይ እንደማለደ ሁላችንም (ኦርቶዶክሱም ፕሮቴስታንቱም) እናምናለን፡፡ ይህ የመስቀሉ የመማለድ ስራ ለዘለአለም ያማልዳል ብሎ በመስቀሉ ስራ መታመን ኦርቶዶክሶች እንደሚመስላቸው በየቀኑ ወደ አብ እየገባ ይለምናል ማለት አይደለም።
ኢየሱስ ከሞት ባይነሳ እና ደሙን ይዞ ወደ አብ ቀኝ ባይገባ መስቀል ላይ የማለደልን ምልጃ ፍጻሜውን አያገኝም ነበር። በራሱ ደም በትንሳኤ አካል ተነስቶ ሕያው ሆኖ እንደሊቀካህን በራሱ ደም ወደ ሰማያዊቷ ቅድስተ ቅዱሳን እኛን ወክሎ አንዴ ሲገባ በዚህ የማስታረቅ አገልግሎት በሆነው በመስቀል ላይ በተሰራው የመማለድ ስራ ለሚመካ ሊቀካህኑ በሕይወት እስካለበት ዘመን ሁሉ ክህነቱ ከመኃላ ጋር ይሰራል፡፡ ኢየሱስ መስዋዕት የመሆንና ወደ ሰማያዊቷ ቅድስተ ቅዱሳን በገዛ ደሙ የመግባትን የሊቀካህንነት ስራውን ጨርሶ በአብ ቀኝ እንደ መልከጸዴቅ ሹመት ከመኃላ ጋር ተወክሎልናል።
ኦርቶዶክሶች ግን ሊቀካህንነቱ ምድር ላይ እንዳበቃ አሁን ሊቀካህናችን ነው ብንል አንድ የኦርቶዶክስ ጸሐፊ እንዳለው ‹‹በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ኢየሱስ ዛሬም በክህነት ያገለገላል ብሎ ማመን የቀራንዮ መስዋዕቱንና የክህነት አገልግሎቱን ከንቱ ማድረግ ነው!›› እንዳለው አይማልድም ብለው ያምናሉ፡፡ ነገር ቃሉ በዕብ.5፡8-10 ‹‹ምንም ልጅ ቢሆን ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤ ከተፈጸመም በኃላ በእግዚአብሔር እንደ መልከጸዴቅ ሹመት ሊቀካህናት ተብሎ ስለተጠራ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘለአለም መዳን ሆነላቸው፡፡›› ይላል፡፡ ኦርቶዶክሶች ኢየሱስ አሁንም ሊቀካህናችን እንደሆነ የማይቀበሉት ለመማለድ አሁንም መለመን ያስፈልገዋል ብለው ስለሚያስቡ ነው፡፡ በተቃራኒው ግን ቃሉ ኢየሱስ እንደ መልከጸዴቅ ሹመት ሊቀካህን የሆነው መከራው ከተፈጸመ በኃላ እና ለዘለአለም ጭምር እንደሆነ ይነግረናል፡፡ ኦርቶዶክሶች ሊረዱ የሚገባቸው ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በመማለድ ይህንን መስዋዕት ወደ አብ ቀኝ ይዞ የገባ እና የክህነት ስራው የተጠናቀቀ እና መስዋዕቱ ተቀባይነት አግኝቶ እግዚአብሔር በኢየሱስ የማስታረቅ አገልግሎት መርካቱን ሲሆን ይህ የመማለድ ስራ እውቅና በማግኘቱ ከመኃላ ጋር ለዚህ የመስቀሉ ስራ(ስም) ከስሞች ሁሉ በላይ የሆነውን ስም በመስጠት በሊቀካህነት ሹመት አጽድቆታል፡፡ ስለዚህ በአብ ቀኝ ሆኖ አሁን አይለምንም የሚለው ቃል ለመቀበል ሲባል ይሄን ቃል መሻር አያስፈልግም፡፡ በእርግጥም ወደ አብ ቀኝ ከገባ በኃላ ልመናን እንደማያቀርብልን ቃሉም ብሎናል እኛም እናምናለን፡፡ ልመና አያቀርብም የተባለውም አንድ ጊዜ መስቀል ላይ በኢየሱስ (በሊቀካህኑ) የተሰራው የመማለድ ስራ ሊቀካህኑ በህይወት ባለበት(ለዘለአለም) ለሚታመንበት የመማለድን ስራ ይሰራልና ነው፡፡ በመስቀሉ ስራ መታመን ማለትም ይህ ነው፡፡
ይሄንን ቃል እስቲ በድጋሚ በጥንቃቄ እናንብበው፡፡
ዩሐ.16፡26 ላይ ‹‹በዚያን ቀን በስሜ ትለምናላችሁ፤ እኔም ስለእናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም፤ እናንተ ስለወደዳችሁኝ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣሁ ስላመናችሁ አብ እርሱ እራሱ ይወዳችኃልና››
27 views06:22
Open / Comment
2022-02-10 12:17:20
𝔽𝕣𝕚𝕕𝕒𝕪 ℕ𝕚𝕘𝕙𝕥

Prayer Night
ዓርብ የካቲት 04
11:30 (Local time)
ዩጎ ቸርች
𝕁𝕖𝕤𝕦𝕤 𝕀𝕤 𝕄𝕠𝕣𝕖 𝕋𝕙𝕒𝕟 𝔼𝕟𝕠𝕦𝕘𝕙!
233 viewsedited  09:17
Open / Comment
2022-02-09 09:03:07 Testimony by Pastor Zerubbabel

A Devotional for February 9, 2022
Ps.100; 1Thes.5:16-18
I have so many testimonies. My testimony actually begins with my father, who was healed of leukemia through an encounter with the Scriptures as a teenager. It’s safe to say I would not be here today if it was not for that! But of all of my experiences in God, there is one that has been most impactful for me.

My early days of ministry were tough. It seemed like God’s promises worked for everyone but me. I was faced with challenges on every side—from finance to family, from ministry to finance…did I mention finance? I could relate well with the words of David in Ps.73:3: “For I envied the arrogant when I saw the prosperity of the wicked. They have no struggles…” They have no struggles?!? What?!?! This disparity became the chief subject of all my prayers.

One day I was watching Christian tv, and a pastor named Phil Munsey came on. He said, “The protocol for entering into His presence is not complaining or prayer requests. Psalm 100 tells us that we enter into His gates with thanksgiving…” I knew the Lord was speaking. I went upstairs to the bathroom, closed the door, and got on my knees. I put all my issues to the side and began to “enter in” with thanksgiving. Then something happened.

Almost immediately, I felt a wind blowing in my face, and the presence of God was so heavy and tangible all around me. For the next two months, I would come home every evening, go to the bathroom and get on my knees, and every evening He would visit me. I had known the Word of God my whole life, but in that season I came to know the God of the Word.

The testimonies I have experienced since then are many—too many to count. But what I learned on that day has been my guiding light: We don’t enter His gates with complaining. We enter His gates with thanksgiving. 1Thes.5:18 reminds us that we don’t give thanks for everything, but in everything; “for this is God’s will for you in Christ Jesus.”

Life Application
Regardless of your situation, start with thanksgiving.

Prayer
Father, in everything I choose to give thanks. Amen

If you have any prayer requests, please write to us on @bezaconnect.
268 views06:03
Open / Comment
2022-02-05 13:37:06
252 views10:37
Open / Comment