Get Mystery Box with random crypto!

Corporate Lawyer

Logo of telegram channel henoktayelawoffice — Corporate Lawyer C
Logo of telegram channel henoktayelawoffice — Corporate Lawyer
Channel address: @henoktayelawoffice
Categories: Loans, Taxes and Laws
Language: English
Subscribers: 461
Description from channel

⌚️10-11
⚖️" "⚖️

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 5

2022-04-30 13:53:11 ስለ መድን ውል- የሰበር ችሎት የህግ ትርጉም
========================
የመድን ውል አመሰራረትና አፈጻጸምን አስመልክቶ የሰበር ችሎት በበርካታ መዝገቦች የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በከፊሎቹ ላይ የተሰጠው የህግ ትርጉም እና የህግ ትንተና እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

1. የመድን ውል አመሰራረት

የመድን ውል ሲመሰረት እንደማንኛውም የውል አቀራረብና አቀባበል /offer and acceptance/ ሊኖር የሚገባ ሲሆን የውል አቀባበል /offer/ የሚከናወነው ደግሞ መድን ገቢው በመድን ሰጭው የሚዘጋጅን መግለጫ /proposal form/ ሲሞላና ይህንኑ መግለጫም ለመድን ሰጭው ሲያስረክብ ነው፡፡ በመድን ገቢው የቀረበው የውል አቀራረብ ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ለማለት የሚቻለው ደግሞ መድን ሰጭው በተዘጋጀው ፖሊሲ ላይ በሚፈርምበት ጊዜ /The issuance of policy/ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ በሁለቱ ወገኖች መካከል የመድን ውል የተቋቋመ በመሆኑ የትኛውም ወገን ሊያቋርጠው አይችልም፡፡

መድን ሰጪው በሚያዘጋጀው ፖሊሲ ላይ መድን ሰጭው መፈረም እንዳለበት በን/ህ/ቁ. 657 ከመመልከቱ በስተቀር መድን ገቢው መፈረም እንደሚገባው ያልተመለከተ በመሆኑ በውል ማቅረቢያ /offer/ ሰነዱ ላይ መድን ገቢው ከፈረመና በፖሊሲው ላይ ደግሞ መድን ሰጭው ከፈረመ በሁለቱ መካከል የመድን ውል ስለመደረጉ በቂ አስረጂ እንደሆነ ከንግድ ህጉ አኳያ መገንዘብ ይቻላል፡፡

ሰ/መ/ቁ. 24703 ቅጽ 7፣[1] ሰ/መ/ቁ 78180 ቅጽ 15፣[2] ን/ህ/ቁ. 651፣ 654፣ 657

2. የውሉ መሻሻል

የኢንሹራንስ ፖሊሲ ተጨማሪ በሆነ ጽሑፍ ካልሆነ በቀር ሊለወጥ እንደማይችል የን/ህ/ቁጥር 657(2) አስገዳጅነት ባለው መልኩ ደንግጓል፡፡ የዚሁ አንቀጽ ንዑስ ቁጥር ሲታይም ፖሊሲው ወይም የፖሊሲው ተጨማሪ ጽሁፍ ከመፈረሙ በፊት ለጊዜው ኢንሹራንስ ሰጪው ኢንሹራንስ ለሚገባው ሰው ፖሊሲው ወይም ለፖሊሲው ተጨማሪ ጽሑፍ እስከ ተፈረመ ድረስ ማረጋገጫ መድን የሚሆነው ጽሑፍ የሠጠው እንደሆነ ኢንሹራንስ ሰጪውና ኢንሹራንስ ገቢው አንዱ ለአንዱ ግዴታ እንደገቡ ይቆጠራል በሚል ይደነግጋል፡፡ የዚህ ድንጋጌ አይነተኛ ዓላማም ውሉ ስለመኖሩ የሚረጋገጠው በጽሑፍ በሆነ ሰነድ መሆኑን ማሳየት ነው ተብሎ ይታመናል፡፡

ሰ/መ/ቁ 78180 ቅጽ 15፣[3] ን/ህ/ቁ. 657(2)

3. የመድን ሰጪው ኃላፊነት

ኢንሹራንስ የተገባለት መኪና በህግ ከተፈቀደው ቁጥር በላይ ተሳፋሪዎች ጭኖ ሲጓዝ ለደረሰበት አደጋ መድን ገቢው የዋስትና ሽፋን ገንዘብ የመክፈል ግዴታ የለበትም፡፡

የንብረት ኢንሹራንስ ውል ከተለያዩ የውል አይነቶች አንዱ ሲሆን ውሉም ህጋዊ የሆኑ ተግባራት በሚከናወኑበት ጊዜ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት በዋስትናው ሽፋኑ መሰረት ለመካስ በማሰብ ሊደረግ የሚገባ ነው፡፡ በፍ/ህ/ቁ. 1678 (ለ) እንደተመለከተው አንድ ውል በቂ የሆነ እርግጠኛነት ያለውና ህጋዊ የሆነ ጉዳይ ለማከናወን ሊደረግ ይገባል፡፡ ህጋዊ ውል የሚደረገው በህግ እንዲደረግ ያልተፈቀደውን ድርጊት ወይም የህግ ክልከላ የተደረገበትን ጉዳይ በማከናወን ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ወይም በሚኖረው ፍላጎት መነሻ ሊሆን አይገባም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 90793 ቅጽ 15፣[4] ፍ/ህ/ቁ. 1678

መድን የተገባለት ተሳቢ መኪና በሌላ ተሳቢ ከተቀየረ ተሳቢው ለሚደርስበት ሆነ ለሚያደርሰው ጉዳት ኢንሹራንስ ሰጭው ኃላፊነት የለበትም፡፡

ኢንሹራንስ ሰጭው በውሉ ለተመለከተው አደጋ ብቻ መድን ለገባው ሰው መድን እንደሚሆን በንግድ ሕግ ቁጥር 663 ንዑስ አንቀጽ 1 ተደንግጓል፡፡ እንደዚሁም ኢንሹራንስ ሰጭው በውሉ ውስጥ የተመለከተው አደጋ በደረሰ ጊዜ ወይም በውሉ የተስማሙበት ቀን በደረሰጊዜ የተስማሙበትን ገንዘብ የመክፈል ግዴታ እንዳለበትና ይህ ግዴታው በውለታው ከተጠቀሰው ሊበልጥ እንደማይችል “የኢንሹራንስ ሰጭው ግዴታ” በሚል ርዕስ ባለው በንግድ ሕግ ቁጥር 665 ተደንግጓል፡፡

ሰ/መ/ቁ 76977 ቅጽ 14፣ ን/ህ/ቁ. 663/1/፣ 665

መድን የተገባለት መኪና የሾፌሩ ረዳት መንጃ ፈቃድ ሳይኖረው የመኪናውን ቁልፍ ሰርቆ ሲያሽከረክር አደጋ ከደረሰ መድን ሰጪው ካሳ የመክፈል ኃላፊነት የለበትም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 50199 ቅጽ 12[5]

ለጭነት ተሽከርካሪ የመድን ሽፋን የሰጠ የኢንሹራንስ ድርጅት በመኪናው ላይ ተሳፍሮ ጉዳት ለደረሰበት ሰው ተጠያቂነት የለበትም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 42139 ቅጽ 9[6]

መድን ሰጪው እና መድን ገቢው ቀደም ብሎ የተደረገና ለረጅም ጊዜ ጸንቶ የቆየ የውል ግንኝኑነት ቢኖራቸውም አደጋው በደረሰበት ዕለት የመድን ውሉ በህጉ አግባብ ካልታደሰ መድን ሰጪው ካሳ የመክፈል ኃላፊነት ይቀርለታል፡፡

የንግድ ህግ ቁ. 666 ተፈጻሚ የሚሆነው የፀና የመድን ውል ኖሮ መድን ገቢው አረቦን ሳይከፍል ከቀረ ነው፡፡ በድንጋጌው መሰረት አረቦን አለመክፈል መድን ገቢውን ከተጠያቂነት አያድንም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 52910 ቅጽ 10፣ ን/ህ/ቁ. 666

4. የካሳው መጠን

የንብረት ኢንሹራንስ ሽፋን የተሰጠው ንብረት ሙሉ በሙሉ ከወደመ መድን ገቢው ሊያገኝ የሚችለው ካሳ ንብረቱ በወደመበት ጊዜ የነበረውን ዋጋ ነው፡፡ ይህም መድን ውሉ ላይ ከተመለከተው የገንዘብ መጠን ሊያንስ ይችላል፡፡

የንግድ ሕግ አንቀጽ 665 በአጠቃላይ ጉዳት ለመካስ ወይም ለመተካት እና ለሰዎች ኢንሹራንስ ላይ ተፈፃሚነት ያለው ጠቅላላ ድንጋጌ ሲሆን፣ በይዘቱ የመድን ሽፋን የሚሰጠው የኢንሹራንስ ኩባንያ ለመዴን ገቢው ወይም ለተጠቃሚው ሊከፍለው የሚችለው ወይም ሊከፍለው የሚገባው የኢንሹራንስ ገንዘብ በመድን ውሉ ከተገለፀው ልበልጥ የማይችል መሆኑን የሚያሣይ ነው፡፡

ንግድ ሕግ አንቀፅ 678 ስለ ንብረት የተደረገ ኢንሹራንስ ውል የሚኖረውን ውጤት በልዩ ሁኔታ የሚደነግግ የሕግ ድንጋጌ ነው፡፡ በመርሕ ደረጃ ለንብረት የሚሰጥ የኢንሹራንስ ሽፋን አደጋው በደረሰበት ጊዜ ንብረቱ የነበረውን ዋጋ የሚያካክስ መሆን እንዳለበት የሚደነግግ ነው፡፡ በንብረት የሚደረግ ኢንሹራንስ መሠረታዊ ዓላማው ንብረቱ በመጎዳቱ ወይም ንብረቱ በመውደሙ በባለንብረቱ ላይ የደረሰውን ኪሣራ ለመተካት ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 69966 ቅጽ 13፣[7] ሰ/መ/ቁ. 48698 ቅጽ 10፣[8] ን/ህ/ቁ. 665፣ 678

በሶስተኛ ወገኖች ላይ ለሚደርስ የአካል ወይም የሞት አደጋ የመድን ሽፋን የሰጠ የመድን ድርጅት በካሳ ረገድ የተጠያቂነት ወሰኑ በውሉ ላይ ከተመለከተው የገንዘብ መጠን ሊያልፍ አይችልም፡፡

ሰ/መ/ቁ. 46808 ቅጽ 10፣[9] ን/ህ/ቁ. 665/2/

መድን ሰጪው በአደጋ ምክንያት ለታጣ ወይም ለተቋረጠ ጥቅም ካሳ የመክፈል ግዴታ ባይኖርበትም መድን የተገባለት ንብረት አደጋ ሲደርስበት ምክንያታዊ በሆነ ጊዜ ውስጥ በመድን ውሉ መሰረት ግዴታውን ካልተወጣ በመድን ገቢው ላይ ለሚደርሰው ኪሳራ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም መድን ገቢው ኪሳራ የመቀነስ ተነጻጻሪ ግዴታ ያለበት በመሆኑ መድን ሰጪው ሊከፍል የሚገባው የካሳ መጠን መኪናውን ለማስጠገን ለሚያስፈልገው ጊዜ ለደረሰው ኪሳራ ብቻ ነው፡፡

ሰ/መ/ቁ. 47076 ቅጽ 12፣[10] ፍ/ህ/ቁ. 1790፣ 1791፣ 1802

5. ይርጋ

አረቦን እንዲከፈል የሚቀርብ ክስ በሁለት ዓመት ይታገዳል፡፡
1.6K views10:53
Open / Comment
2022-04-18 13:39:02 2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት በጡረታ ለሚሰናበት የመንግሥት ሠራተኛ ጡረታ ከመውጣቱ ከሶስት ወር በፊት በጽሑፍ እንዲያውቀው ይደረጋል፡፡
አንቀጽ 90፡- በሞት ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ከሞተበት ቀን ጀምሮ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. አገልግሎቱ በሞት ምክንያት የተቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ የሞተበት ወር ሙሉ ደመወዙ እንዲሁም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 41(1) መሠረት ላልተወሰደ የዓመት ዕረፍት ፈቃድ የሚፈጸም ክፍያ ለትዳር ጓደኛው፣ የትዳር ጓደኛ ከሌለው ለሕጋዊ ወራሾች ይከፈላል፡፡
3. አግባብ ባለው የጡረታ ህግ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በሞት ምክንያት አገልግሎቱ ሲቋረጥ ለሚሠራበት መሥሪያ ቤት በጽሑፍ ላሳወቃቸው የትዳር ጓደኛው ወይም በስሩ ይተዳደሩ ለነበሩ ቤተሰቦች የሦስት ወር ደመወዝ በአንድ ጊዜ ይከፈላል፤ ሆኖም የትዳር ጓደኛውን ወይም በሥሩ የሚተዳደሩ ቤተሰቦቹን ሳያስመዘግብ የሞተ እንደሆነ ሥልጣን ካለው አካል ወይም ፍርድ ቤት በሚሰጥ ማስረጃ መሠረት ክፍያው ይፈጸማል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት የሚሰጠው ክፍያ ከግብርና ከጡረታ መዋጮ ነጻ ይሆናል፤ እንዲሁም በዕዳ ሊከበር ወይም በማቻቻያነት ሊያዝ አይችልም፡፡
አንቀጽ 91፡- የአገልግሎት ምስክር ወረቀት አሠጣጥ/Certificate of Service/ ክሊራንስ/
1. ለማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የሚሰጥ የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት ሠራተኛው ሲያከናውን የነበረውን የሥራ ዓይነት፣ የአገልግሎት ዘመኑና ሲከፈለው የነበረውን ደመወዝ የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
2. የሥልጠና ውል ግዴታ ወይም በመንግሥት መሥሪያ ቤቱ የሚፈለግበት ማናቸውም ዕዳ ያለበት የመንግስት ሠራተኛ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎቱን ሲያቋርጥ የውል ግዴታውን ስለመፈጸሙ ወይም ከዕዳ ነጻ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ከማግኘቱ በፊት የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት አይሰጠውም፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) በሥራ ላይ እያለ የሥራ ልምድ የምስክር ወረቀት ለሚጠይቅ የመንግስት ሠራተኛ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡
አንቀጽ 92፡-አገልግሎት ሲቋረጥ የሚፈጸም ክፍያ
1. የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 87 መሠረት በቅነሳ ምክንያት ከሥራ ከተሰናበተና የሥራ ውሉ በተቋረጠበት ዕለት የጡረታ አበል የማይከፈለው ከሆነ፣
1.1. ለመጀመሪያ አንድ ዓመት የሦስት ወር ደመወዝ፣
1.2. በተጨማሪ ለአገለገለበት ለእያንዳንዱ ዓመት የወር ደመወዙ አንድ ሦስተኛ እየታከለ፣ ይከፈለዋል፤ ሆኖም የሚሰጠው ክፍያ ከሠራተኛው የአሥራ ሁለት ወር ደመወዙ መብለጥ የለበትም፡፡
2. የሙከራ ጊዜውን ለጨረሰና ከአንድ ዓመት በታች ላገለገለ የመንግስት ሠራተኛ የሚፈጸመው ክፍያ ከአገልግሎቱ ጋር ተመጣጣኝ ይሆናል፡፡
አንቀጽ 93፡- አገልግሎትን ማራዘም
1. የመንግሥት ሠራተኛ የመጦሪያ ዕድሜው ከደረሰ በኋላ በአንድ ጊዜ እስከ አምስት ዓመት በጠቅላላው ከአሥር ዓመት ለማይበልጥ ጊዜ አገልግሎቱን ማራዘም ይቻላል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የአንድን የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎት ማራዘም የሚቻለው፣
2.1. የሠራተኛው ትምህርት፣ ልዩ ዕውቀትና ችሎታ ለመሥሪያ ቤቱ ሥራ ጠቃሚ ሆኖ ሲገኝ፣
2.2. በደረጃ ዕድገት፣ በዝውውር ወይም በቅጥር ተተኪ ሠራተኛ ለማግኘት አለመቻሉ ሲረጋገጥ፣
2.3. ሠራተኛው ለሥራው ብቁ መሆኑ በሕክምና ማስረጃ ሲረጋገጥ፣
2.4. ሠራተኛው አገልግሎቱን ለመቀጠል ሲስማማ፣ እና
2.5. የአገልግሎቱ መራዘም ጥያቄው የመጦሪያ ዕድሜው ከመድረሱ ከሦስት ወር በፊት ለሚኒስቴሩ ቀርቦ ሲፈቀድ፣ ነው፡፡
የመንግስት ሰራተኛ አዋጅን በቴሌግራም ያግኙ

በቴሌግራም ተጨማሪ መረጃ ያግኙ


Source legal consulting limitedsa
551 viewsedited  10:39
Open / Comment
2022-04-18 13:39:01 የሥራ ውል ማቋረጥና ማራዘም /የመንግስት ሠራተኛ/

በባለፈው ጽሑፍ አንድ መንግስት ሠራተኛ እንዴት ከሥራ ልታገድ ይችላል በሚል ፖስት ካደረኩ በኋለ ብዙ ሰዎች ከሥራችሁ ጋር ብዙ ጥያቄ ያቀረባችሁ ሲሆን ለእያንዳንዱ መልስ መስጠት ወይም በስልክ ማስረዳት ጊዜ ስለሚወስድ በቂም ላይሆን ስለሚችል በሚከተለው መልኩ እንድትረዱና አስፈላጊውን መረዳት እንድታገኙ ቀርቦላችኋል፡- የፌደራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064 የህግ ድንጋጌዎች /የተወሰኑ ማብራሪያ ብቻ ተደርጎ/
አንቀጽ 83፡- በራስ ፈቃድ የሥራ ውል ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በማንኛውም ጊዜ የአንድ ወር ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሥራውን በፈቃዱ ሊለቅ ይችላል፤ ሆኖም መስሪያ ቤቱ ሠራተኛውን በቀላሉ ሊተካው የሚችል ከሆነ የአንድ ወሩን ጊዜ ሳይጠብቅ ስንብቱን ሊፈቅድለት ይችላል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተውን የአንድ ወር የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ አገልግሎቱን ያቋረጠ የመንግሥት ሠራተኛ ግዴታውን ባለመወጣቱ ለሚደርሰው ጉዳት እንደተገቢነቱ በፍትሐ ብሔር እና በወንጀል ሕግ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
3. የመንግሥት ሠራተኛው ለሥራው እጅግ አስፈላጊና በቀላሉ ለመተካት የማይቻል ሆኖ ሲገኝ ወደ ፊት ከሚቀጠርበት መስሪያ ቤት ጋር በመስማማት የመልቀቂያውን ጥያቄ ሠራተኛው ካመለከተበት ቀን ጀምሮ ከሦስት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ሊራዘም ይችላል፡፡
አንቀጽ 84፡- በሕመም ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 43(2) ወይም (4) በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ለመመለስ ካልቻለ በሕመም ምክንያት አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. የዚህ አዋጅ አንቀጽ 59(3) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ በሥራው ምክንያት ጉዳት የደረሰበት የመንግሥት ሠራተኛ ለዘለቄታው መሥራት አለመቻሉ በሕክምና ማስረጃ ሲረጋገጥ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
3. በዚህ አዋጅ አንቀጽ 26 ንዑስ አንቀጽ (3)(ለ) መሠረት በሚፈጸመው ዝውውር ተስማምቶ ለመስራት ፈቃደኛ ያልሆነ የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 85፡- በችሎታ ማነስ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
1. የሙከራው ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግስት ሠራተኛ በሥራ አፈጻጸም ውጤቱ የችሎታ ማነስ ከታየበት ተገቢው የአቅም ማጎልበት ሥልጠናዎች ተሰጥተውት ካልተሻሻለ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
2. የመንግሥት ሠራተኛ ያለውን ዕውቀትና ችሎታ እየተጠቀመ በተመደበበት ሥራ ላይ የሥራ አፈጻጸም ውጤቱ በተከታታይ ለሶስት ጊዜ ከሚጠበቀው ውጤት በታች ከሆነ በችሎታ ማነስ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ ቢኖርም ለተከታታይ አምስት ዓመታት ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤት ሲያገኝ የነበረ የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ውጤቱ በተከታታይ ለአራት ጊዜ ከሚጠበቀው ውጤት በታች ካልሆነ በስተቀር ከሥራ አይሰናበትም፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) እና (3) መሠረት የመንግሥት ሠራተኛውን ከሥራ ማሰናበት የሚቻለው እንደአስፈላጊነቱ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 31 ላይ የተቀመጠውን የሥራ አፈጻጸም ምዘና ዓላማ በመከተል ይሆናል፡፡
አንቀጽ 86፡- ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
1. የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ምክንያቱን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለመሥሪያ ቤቱ ማሳወቅ አለበት፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ሪፖርት የተደረገለት የመንግሥት መሥሪያ ቤት የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሠራተኛው ከሥራ ገበታው ላይ የተለየበት ምክንያት ከአቅም በላይ መሆኑን ካረጋገጠ የመንግሥት ሠራተኛው ይዞት የነበረውን የሥራ መደብ ለስድስት ወር ክፍት አድርጎ መጠበቅ አለበት፡፡ ሆኖም የመንግሥት ሠራተኛው በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራው ካልተመለሰ ከሥራ ማሰናበት ይቻላል፡፡
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ ቢኖርም የመንግስት ሰራተኛው ከስድስት ወር በላይ በሥራ ላይ ያልተገኘው በእስር ምክንያት ከሆነና ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት በነፃ ስለመለቀቁ ማስረጃ ካቀረበ የመንግስት መስሪያ ቤቱ ባለው ክፍት የሥራ መደብ ቀደም ሲል ይከፈለው የነበረውን ደመወዝ እያገኘ ወደ ሥራ እንዲመለስ ማድረግ አለበት፡፡
4. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለተከታታይ አሥር ቀናት ከመደበኛ የሥራ ቦታው ላይ ከተለየ በየአስር ቀናት ልዩነት በተከታታይ ለሁለት ጊዜ በማስታወቂያ ተጠርቶ ለመንግስት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካላደረገ ከሥራ ይሰናበታል፡፡
5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (4) መሠረት በማስታወቂያ ጥሪ የተደረገለት የመንግሥት ሠራተኛ ከሥራ ከተለየበት ቀን ጀምሮ አንድ ወር ከመሙላቱ በፊት ወደ ሥራው ለመመለስ ለመንግስት መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ሠራተኛው ከሥራ የቀረበትን ምክንያት በመመርመር የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ወደ ሥራው እንዲመለስ ይደረጋል፡፡
6. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (4) ቢኖርም ከስራ የተሰናበተ ሰራተኛ ከሥራ ከቀረበት ቀን ጀምሮ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ከሥራ የቀረበት ምክንያት ከአቅም በላይ ለመሆኑ ለመሥሪያ ቤቱ ሪፖርት ካደረገና በቂ ማስረጃ ካቀረበ በመሥሪያ ቤቱ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ የመሥሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወይም ተወካዩ ሲፈቅድ ወደ ሥራ ሊመለስ ይችላል፡፡
7. የሙከራ ጊዜውን ያላጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ባልታወቀ ምክንያት ለአንድ ወር ጊዜ በሥራ ገበታው ላይ ካልተገኘ ያለተጨማሪ ሥነ-ሥርዓት አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 87፡- የሠራተኛ ቅነሳ
1. ማንኛውንም የመንግሥት ሠራተኛ፣
ሀ) የሥራ መደቡ ሲሰረዝ፣
ለ) መሥሪያ ቤቱ ሲዘጋ፣
ሐ) ትርፍ የሰው ኃይል ሲኖር፣
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 30(1) መሠረት ለመደልደል ካልተቻለ ወይም የመንግሥት ሠራተኛው ዝቅ ባለ የሥራ ደረጃ ላይ ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ ከሥራ ይሰናበታል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1)(ሐ) መሠረት ቅነሳ የሚደረገው የመንግሥት ሠራተኛው በመሥሪያ ቤት ውስጥ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ካሉ ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ጋር ሲወዳደር በሥራ ውጤቱና ባለው ችሎታ ዝቅተኛ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡
አንቀጽ 88፡- በዲስፕሊን ምክንያት ከሥራ ማሰናበት
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 69 ንዑስ አንቀጽ (1)(ሠ) መሠረት በዲስፕሊን ቅጣት የተወሰነበትና በአስተዳደራዊ ይግባኝ ውሳኔው ያልተሰረዘለት የመንግሥት ሠራተኛ አገልግሎቱ ይቋረጣል፡፡
አንቀጽ 89፡- በዕድሜ ምክንያት አገልግሎት ስለማቋረጥ
1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 73 መሠረት አገልግሎቱ ካልተራዘመ በስተቀር በሕግ ከተወሰነው የመጦሪያ ዕድሜ ከደረሰበት የመጨረሻ ወር የመጨረሻ ቀን ጀምሮ አገልግሎቱ እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡
507 views10:39
Open / Comment
2022-04-16 08:32:50
#Ads
ኢትዮጵያ ውስጥ በሕግ ዙሪያ የሚሰሩ ሦስት ትላልቅ የሕግ ቻናሎችን አሁኑኑ ይቀላቀሉ
ለመቀላቀል ከታች የሚገኙትን ማስፈንጠሪዎች ይጠቀሙ
329 views05:32
Open / Comment
2022-04-15 23:33:49 ጉባዔው በ26 የሕገ መንግሥት ትርጉም ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
--------------------------------------------------------------------------------
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ረቡእ ሚያዝያ 05 ቀን 2014 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ 26 ጉዳዮች ላይ በመወያየት 25ቱ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት እንዲዘጉ የወሰነ ሲሆን፤ በአንድ ጉዳይ ላይ በሰፊው በመወያየት ጉዳዩ ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበት በይደር እንዲያልፍ ወስኗል።
ሰፊ ውይይት የተደረገበትና ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበት የተወሰነው ጉዳይ የንብረት ክርክር ጉዳይ ሲሆን ለክርክሩ መነሻ የሆነው ቤት የስምንት ሰዎች ይዞታ የተመዘገበ ሆኖ እያለ ፍ/ቤቱ ከስምንቱ አመልካች አንዱ ሆነው የቀረቡትን የተከሳሽ ሚስትንና ተከሳሽ ሆነው የቀረቡትን ባል በማከራከር የከሣሽ እና ተከሣሽ የጋራ ሀብት ነው በማለት ይወስናል፡፡ የተቀሩት ሰባቱ ባለይዞታዎችም ውሳኔውን በፍ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 358 በመቃወም ጣልቃ ገብ አመልካች ሆነው ወደ ክርክሩ ቢገቡም ፍ/ቤቱ በክርክሩ ሂደት ወቅት ግማሾቹ በምስክርነት የቀረቡ ሌሎቹ ደግሞ ችሎት እየገቡ ሲከታተሉ የነበሩ በመሆኑ መብታቸውን ለማስከበር ጣልቃ በመግባት መከራከር እየቻሉ የክርክሩን ውጤት ጠብቀው መብታቸውን የሚነካ ውሣኔ ሲሰጥ በፍ/ስ/ስ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት ያቀረቡት ተቃውሞ ተቀባይነት የለውም በማለት ብይን ይሰጣል፡፡ የይግባኝ አቤቱታቸውን ለፌ/ከ/ፍ/ቤት ቢያቀርቡም ፍ/ቤቱ አስቀርቦ በማከራከር የስር ፍ/ቤት ውሣኔን አፅንቷል፡፡ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም አያስቀርብም በማለት ጉዳዩን በመዝጋቱ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መ.ቁ. 201187 እና 187023 የሰጣቸው ውሣኔዎች በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40/1፣ 2፣ 7 እና 81 ስር የተደነገጉትን የንብረት መብቶች እና በአንቀጽ 9/1/ የተደነገገውን የሕገ መንግሥት የበላይነት ድንጋጌን ስለሚቃረን የሕገ መንግሥት ትርጉም ይሰጠን በማለት ጠይቀዋል፡፡
ጉባዔውም በጉዳዩ ላይ በስፋት የተከራከረ ሲሆን በአንድ በኩል ከላይ ፀንተው ያሉት ሁለቱ ውሣኔዎች ለሕገ መንግሥት ትርጉም አቤቱታ የቀረቡ ቢሆንም ሁለቱም የፍ/ቤቶቹ ውሣኔዎች ማስረጃን በመመዘን እና ሕግን በመተርጎም የተወሰኑ በመሆናቸው የአመልካቾችን የትኛውንም ሕገ መንግሥታዊ መብት የሚፃረሩ አይደሉም የሚል ሀሳብ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል የፍ/ስ/ስ/ህጉ ቁ. 358 ድንጋጌ ይዘት ሲመረመር በዋና ክርክር ወቅት ተካፋይ መሆን ሲገባው በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነና ወይም በክርክሩ መብት ያለው እና ተካፋይ ባልሆነበት ክርክር የተሰጠው ፍርድ መብቱ የተነካበት ሰው ፍርዱ ከመፈጸሙ በፊት የመቃወም አቤቱታ አቅርቦ መከራከር እንደሚችል በግልጽ ስለሚገነግግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 56795 ላይ አንድ ክርክር መጀመሩን ያወቀ ወገን የክርክሩን ውጤት ጠብቆ መብቱን የሚነካበት ሆኖ ባገኘው ጊዜ ከውሳኔው በኋላ የሚያቀርበው አቤቱታ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 358 መሰረት ተቀባይነት የለውም ብሎ የሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ህግን ከመተርጎም ስልጣኑ ያለፈና የአመልካቾችን ንብረት የማፍራት መብት የሚጻረረር በመሆኑ ውሳኔው የሕገ መንግስቱን አንቀጽ 37፣ 40 እና 79(1) ድንጋጌ ስለሚቃረን የሕገ መንግሥት ትርጉም ያስፈልገዋል የሚል ሀሳብ ቀርቧል፡፡ ጉባዔውም በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ጥናት እንዲደረግበትና ለቀጣይ ውይይት እንዲቀርብ ወስኗል፡፡
321 views20:33
Open / Comment
2022-04-15 16:57:26
1.2K views13:57
Open / Comment
2022-04-15 16:15:56 ባንኮች ባገኙት ንፋስ አመጣሽ ገቢ ላይ ግብር የሚከፈልበትን ሁኔታ
ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 238/2013
1.2K views13:15
Open / Comment
2022-04-14 14:23:02 አዲሱ የንግድ ሕግ ትግበራን በተመለከተ የተሰጠ ስልጠና
Credit - Click Ethiopia laws
1.8K views11:23
Open / Comment
2022-04-13 12:51:10 የክስ ምክንያት ምንድነው?
#Like #Comment #Share ያድርጉ

ለጥያቄው ምላሽ የሰበር ችሎት በ 6 መዝገቦች ላይ እንደሚከተለው የህግ ትርጓሜ ሰጥቷል።

1/ አንድ ሰው አንድን ነገር ከአንድ ሰው ላይ ለማግኘት ፍ/ቤቱ እንዲወስንለት ክስ ለማቅረብና ዳኝነት ለማግኘት የሚያስችለው የፍሬ ነገር ሁኔታ

ማንም ሰው በህግ ችሎታ ኖሮት በሌላ ሰው ላይ ማናቸውንም ክስ ለማቅረብ እንዲችል አስቀድሞ ለክሱ መነሻ በሆነው ነገር ወይም ክሱ በተመሠረተበት ነገር ላይ ጥቅም ወይም መብት ያለው መሆኑ መረጋገጥ እንደሚገባው የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 33 ይደነግጋል፡፡ በዚህም ከሣሽ ከተከሣሽ ላይ ሊፈፀም የሚችል መብት አለኝ ብሎ ለማለት አስቀድሞ ለመብቱ መገኘት መነሻ የሆነውን ነገር በማረጋገጥ የተጠየቀውን ዳኝነት ለማግኘት ከሣሹ በሕግ መብት ያለው መሆን ይኖርበታል፡፡
የክስ ምክንያት አለ ብሎ ለመወሰን የሚቻለው በክሱ ላይ የቀረበው ነገር ቢረጋገጥ ከሣሹ የጠየቀውን ዳኝነት ለማግኘት ሕግ ይፈቅድለታል ወይ? ለሚለው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ሲቻል ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 16273 ቅጽ 2፣ ስለ አሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣ አዋጅ ቁ. 42/85 አንቀጽ 9፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 29፣ 80/2/፣ 224/2/፣ 23/1/ ሀ ፣ 224/2/፣ 23/1//ሀ/፣ 33፣ ሮበርት አለን ሴድለር በችሎቱ እንደተጠቀሰ

2/ ሻጭ ከሽያጭ ውሉ በሚመነጭ ግዴታ የተሸጠውን ነገር ስመ ሀብትነት በሚመለከተው ክፍል ቀርቦ ለማዛወር እንደገባው ግዴታ ይፈጽምልኝ የሚል ክስ የክስ ምክንያት አለው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 82234 ቅጽ 15

3/ አንድ ክስ ሊቀርብ የሚገባው የክስ ምክንያት ሲኖረው ሲሆን የክስ ምክንያትም ተከሣሽ ለከሣሽ ሊፈጽመው የሚገባው ግዴታ መኖሩ ጋር ተያይዞ ሊነሣ የሚችለውን ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ መስጠት የሚቻልበት ሁኔታ ስለመኖሩ ሲረጋገጥ የሚታወቅ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ. 33945 ቅጽ 12፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 231(1) ሀ

4/ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት
በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 231 ላይ እንደተመለከተው ማንኛውም ፍርድ ቤት የክስ አቤቱታ ሲቀርብለት ተከሣሽ የሆነው ወገን ክሱን እንዲከላከል ከመጥራቱ በፊት ከሳሽ ክሱን ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት ያለው ስለመሆኑና ፍ/ቤቱም አቤቱታውን ተቀብሎ ለማየት ስልጣን ያለው ስለመሆኑ መመርመር ይኖርበታል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 32147 ቅጽ 6፣ ፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 231

5/ አንድ ሰው በተለያዩ ምክንያቶች በአባቱ ብቻ ሳይሆን በአሳዳጊው ስም ጭምር ሊጠራ የሚችልባቸው አጋጣሚዎች መኖራቸው የሚታወቅ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ ሰው ተገቢ ሆኖ ባገኘው ጊዜ በአሳዳጊው ስም ጭምር መጠራቱ ቀሪ ሆኖ በፍትሐብሔር ሕጉ መሰረት በአባቱ ስም ብቻ እንዲጠራ የመወሰን መብት ያለው በመሆኑ ይህንኑ መብቱን በፍርድ ለማረጋገጥ የሚያቀርበው የዳኝነት ጥያቄ የክስ ምክንያት የለውም የሚባልበት ሕጋዊ ምክንያት አይኖርም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 95995 ቅጽ 15

6/ ከባዶ ቦታ ሽያጭ የመነጨ ግዴታ ለማስፈጸም የሚቀርብ አቤቱታ የክስ ምክንያት የለውም፡፡
ሰ/መ/ቁ. 27739 ቅጽ 6
@henoktayelawoffice
በአብርሐም ዮሐንስ
#LegalServices #legalconsulting #lawyer #attorney #attorneyatlaw #lawstudent #Ethipianlawstudents #judge #justice#henoktayelawoffice
2.4K views09:51
Open / Comment
2022-04-11 15:13:49
3.0K views12:13
Open / Comment