Get Mystery Box with random crypto!

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.34K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 8

2023-06-05 19:07:06 Live stream started
16:07
Open / Comment
2023-06-05 19:05:26 Live stream finished (1 minute)
16:05
Open / Comment
2023-06-05 19:03:37 Live stream started
16:03
Open / Comment
2023-06-05 19:03:20 https://www.facebook.com/dw.amharic/videos/734114315063265/
አፍሪቃ ችሎታ ያላቸው ብስክሌተኞች ቢኖራትም ወደ አውሮጳ እና ሌሎች ትላልቅ ሃገራት ተጉዘው አቅማቸውን ማሳየት ሲቸገሩ ይሰማል። በዚያው ልክ እንደ ኤርትራዊው ቢኒያም ግርማይ ያሉ ደግሞ ከሀገራቸው አልፈው የጥቁር አፍሪቃውያን ኩራት እስከ መሆን የደረሱበትን ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸው ለአፍሪቃውያኑ ጊዜው የደረሰ ይመስላል። አፍሪቃውያኑን ለትላልቅ ዓለማቀፍ ውድድሮች ለማብቃት የሚንቀሳቀስ «የአፍሪቃ ትንሳኤ የተሰኘ » የብስክሌተኞች ቡድን ለአፍሪቃውያኑ ስልጠናን ጨምሮ ቁሳቁስ ለቅረብ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው። ተከታዩ ቪዲዮም በዚሁ ላይ ያተኮረ ነው።
2.8K viewsDW Amharic Team, 16:03
Open / Comment
2023-06-05 19:03:01 Live stream finished (1 minute)
16:03
Open / Comment
2023-06-05 19:01:45 Live stream started
16:01
Open / Comment
2023-06-05 19:00:27 Live stream finished (1 minute)
16:00
Open / Comment
2023-06-05 18:59:24 Live stream started
15:59
Open / Comment
2023-06-05 18:43:18
መቐለን ጨምሮ በበርካታ የትግራይ አካባቢዎች እንዲሁም አዋሳኝ የአፋር እና ኤርትራ አካባቢዎች 4.7 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ ርእደ መሬት ተከሰተ። ተመሳሳይ መጠን ያለው ርእደ መሬት በአካባቢው ሲያጋጥም በአምስት ወራት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ግዜ ነው ተብሏል። ምሁራን ተፈጥሮአዊው ክስተት የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎች በመውሰድ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ መቀነስ እንደሚቻል አሳስበዋል።
በዋነኝነት በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም አዋሳኝ የዓፋርና ኤርትራ ቦታዎች ትላንት የተከሰተው ርእደ መሬት 4.7 ሬክተር ስኬል መመዝገቡን የተለያዩ ዓለምአቀፍ ተቋማት መረጃዎች ያመለክታሉ። የአሜሪካው ስነምድር ጥናት ተቋም USGS ሪፖርት እንደሚያሳየው የርእደ መሬቱ መነሻ ከዓዲግራት ወደ ምስራቅ አቅጣጫ በትግራይ፣ ዓፋር እና ኤርትራ አዋሳኝ አካባቢ መሆኑ የሚገልፅ ሲሆን የርእደ መሬቱ የመሬት ውስጥ ጥልቅ ርቀት ደግሞ 10 ነጥብ 0 ኪሎሜትር ስለመሆኑ ተነግሯል። በትግራይ፣ ዓፋር እና ኤርትራ አዋሳኝ አካባቢዎች ተመሳሳይ መጠን ያለው ርዕደ መሬት ሲከሰት በአምስት ወራት ውስጥ የትላንቱ ለሁለተኛ ግዜ ነው። ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻም እንዲሁ ተመሳሳይ ንዝረት ያለው ርእደ መሬት በአካባቢው ተከስቶ ነበር።
የምሽቱ መጽሔታችን ዝርዝር ዘገባ ይዟል።
2.8K viewsDW Amharic Team, 15:43
Open / Comment
2023-06-05 18:42:49 ...ይህንንም አንድ ወር ባነሰ ግዜ ውስጥ ለማከናወን አቅደንል ወደ ሥራ እየገባን እንገኛለን “ ብለዋል፡፡
ዕዳውን የማስመለሱን ሂደት ሥኬታማ ለማድረግ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ የኮማድ ፖስት ወይንም የዕዝ ሠንሰለት መዋቅር መዘርጋቱን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ ተናግረዋል፡ከተጠያቂነት አንጻር ሂደቱን ለማስስተጓጎል የሚሞክር ማንኛውም አካል በህግ አግባብ እርምጃ የሚወሰድበት ይሆናል ያሉት ኃላፊ “ ለዚህም ዕዳውን የማስፈጸሙ ሂደት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት እና የክልሉን ፍትህ ቢሮ ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጣ ኮማንድ ፖስት እንዲመራ ተደርጓል ፡፡ የኮማንድ ፖስቱ ዋና ዓላማ ገንዘቡን ማስመለስ ነው ፡፡ የሚፈለግባቸውን ገንዘብ በሚያሸሹ ወይም ራሳቸውን ሊያሸሹ በሚሞክሩ አካላት ላይም የተጠናከረ ክትትል ይደረጋል፡፡ ያለባቸውን ዕዳ ሲመልሱም እጃቸው ላይ ካቆዩበት የወለዱ መጠን ጋር የሚመልሱ ይሆናል ›› ብለዋል ፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ደገላ ኤርገኖ የደቡብ ክልልን ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮች በቅርበት ከሚከታተሉት የዘርፉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ናቸው ፡፡ ክልሉ አሁን ላይ ከአፈር ማዳበሪያ ዕዳ አመላለስ ጋር በተያያዘ ባጋጠመው የበጀት መዛባት ዙሪያ በዶቼ ቬለ DW አስተያየታቸውን የተጠየቁት ዶክተር ደገላ የበጀት ክፍተቱ በቶሎ መፍትሄ ካላገኘ በክልሉ ላይ ምጣኔ ሀብታዊና ፖለቲካዊ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል የሚል ሥጋት እንዳላቸው ተናግረዋል ፡፡
በክልሉ መመለስ የነበረበት ዕዳ ወደ መንግሥት ቋት አለመግባቱ ክልሉ ጤናማ በሆነ የበጀት ሥረዓት ውስጥ እንዳይገኝ እንዳደረገው የጠቀሱት ዶክተር ደገላ “ ይህ ሁኔታ አይደልም አንገብጋቢ የድህንት ቅነሳ ሥራዎችን ለማከናወን ቀርቶ በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ለሠራተኞች ደሞዝ መክፈል የማይችልበት ደረጃ ላይ ሊያደርሰው ችሏል ፡፡ የበጀት ክፍተቱን በቶሎ ማስተካከል ካልተቻለ በክልሉ ላይ ተጨማሪ ፖለቲካዊ ተፅኖ ሊያሳድር ይችላል ፡፡ምክንያት ሁኔታው ግብር እየከፈሉ ልማት ያላገኙ ዜጎችን ቅሬታ ውስጥ የማስገባት ዕድሉ ሠፊ ነው ፡፡ ይህም በጊዜ ሂደት አስፈጻሚውን አካል ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ሊከተው ይችላል “ ማለታቸውን የሐዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ዘግቧል ፡፡
በቀጣይ የክልሉ ምክር ቤትና አስፈጻሚው አካል የተጣለባቸውን ሃላፊነት ሊወጡና ተጠያቂነትን ሊያሰፍኑ ይገባል ያሉት የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ደገላ በተለይ በዕዳ አመላለስ ሂደቶችም ሆነ ለወደፊቱ በሚኖረው የበጀት አስተዳደር ሥራ ላይ ክልሉ በፋይናንስ ህግና ደንብ ብቻ እንዲመራ በማድረግ ከችግሩ ሊወጣ የሚችልበት ዕድል መኖሩንም ጠቁመዋል ፡፡
2.7K viewsDW Amharic Team, 15:42
Open / Comment