Get Mystery Box with random crypto!

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.34K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 10

2023-05-17 17:37:07
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ህወሓት ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ የሰላም ሂደቱን ይጎዳል አለ። ህወሓት በበኩሉ የምርጫ ቦርድ ያስተላለፈውን ውሳኔ ዳግም እንዲያጤን ጠይቋል። ጉዳዩን አስመልክቶ ህወሓት ትናንት ባወጣው በዚሁ መግለጫው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ህወሓት፣ ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስለት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረቡን በማመልከት፣ ቦርዱ ግን «ሕጋዊ ሰውነት የመሰረዝ ውሳኔ እንዲያነሳ ያቀረብንለት ጥያቄ የሰላም ስምምነቱ አላማ የሆኑ ሐሳቦችን በሚጻረር ሁኔታ ምላሽ ሰጥቷል» ሲልት ወቅሷል። ህወሓት የቦርዱን ውሳኔ «የሰላም ስምምነቱን የማይቀበል፣ የሰላም ስምምነቱን አተገባበር ባለቤት አልባ የሚያደርግ፣ በቀጣይም ለሰላሙ እንቅፋት የሚፈጥር» በማለትም ተችቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለግዜው ተጨማሪ ማብራሪያ መስጠት እንደማይችል ገልጿል። በዕለቱ የዜና መጽሔት ዝርዝር ዘገባ ተካቷል፤ ጠብቁን። ዶቼ ቬለን ተከታተሉ።
2.9K viewsDW Amharic, 14:37
Open / Comment
2023-05-17 17:15:58
የኦሮሞ ነጻ አውጪ ሠራዊት የመንግሥት ኃይሎች በበርካታ የክልሉ አካባቢዎች መጠነ ሰፊ ጥቃት ከፍተውብኛል አለ። የቡድኑ ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ በትዊተር ገጻቸው ያጋሩት የቡድኑ መግለጫ፤ የታንዛኒያው የሰላም ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ በበርካታ አካባቢዎች የመንግሥት ኃይሎች ጥቃት እንደከፈቱበት አመልክቷል። እንዲህ ያለው እርምጃም በሰላም ውይይቱ ግጭትን ለመቀነስ የተደረሰባቸውን የመግባቢያ ሃሳቦች በእጅጉ የሚጻረር ነው ብሏል። ቡድኑ ለሰላም ካለው ቁርጠኝነት ባሻገርም በምዕራብ ወለጋ፣ በምሥራቅ ወለጋ፤ በሆሮ ጉድሩ፤ በምዕራብ ሸዋ፣ በምሥራቅ ሸዋ፣ በአርሲ፣ በሐረርጌ፣ ቦረና እና ጉጂ ይዞታዎቹን ለመከላከል መገደዱንም አመልክቷል። ቡድኑ በመግለጫው አክሎም በአሁኑ ጊዜ የተከፈተበትን ጥቃትም ለሁለተኛው ዙር ውይይት የበላይነት ይዞ ለመቅረብ ያለመ ነው ብሎታል።እንዲያም ሆኖ በመንግሥትና በቡድኑ መካከል ሁለተኛ ዙር ውይይት መቼ እንደሚካሄድ በመግለጫው አልተጠቀሰም። ታጣቂው ቡድን ያሰማውን ክስ በተመለከተ ከመንግሥት በኩል የተባለ ነገር የለም። እንዲያም ሆኖ የመንግሥት እና የኦሮሞ ነጻ አውጪ ሠራዊት ኃይሎች በሚፋለሙባቸው የተጠቀሱት አካባቢዎች ነዋሪዎች በከፍተኛ ችግር ላይ እንደሚገኙ የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
2.9K viewsDW Amharic, 14:15
Open / Comment
2023-05-17 13:18:22
...በዚህ መነሻነትም ሕገ መንግሥቱ ውስጥ ከመግቢያው አንስቶ አንቀጽ 8 እንዲሁም አንቀጽ 39ኝ ጨምሮ አነጋጋሪ ነጥቦች የሚባሉት ላይ በማተማኮር ጥናቱ መደረጉንም ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። «በአንዳንድ ምሁራን፤ በፖለቲካ ልኂቃን እንዲሁም የማኅበረሰብ አንቂ በሚባሉት በኩል ሕገመንግሥቱን የግጭቶች ሁሉ መነሻ አንድርጎ የመመልከት አዝማሚያ አለ» ያሉት ዶክተር ጥላሁን፤ «ጥናቱ ያሳየው ግን በዚህ ሃሳብ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ስምምነት እንደሌለ ነው» ብለዋል። ጥናቱ የተደረገበት ዋና አላማም መንግሥት ተነስቶ ሕገ መንግሥቱን እቀይራለሁ በሚል ሌላ እርምጃ ውስጥ እንዲገባ ሳይሆን ሕገ መንግሥቱን በሚመለከት በቀጣይ ለሚደረግ ሀገራዊ ውይይትም ሆነ ክርክር ግብአት እንዲሆን ታስቦ መሆኑንም ነው አጽንኦት የሰጡት። በጥናቱ ማጠቃለያ ላይ በሰጡት ምክረ ሃሳብም «መንግሥት ሕገ መንግሥቱ ስለመቀየር ቀነ ገደብ ሁሉ ማስቀመጥ እንደሌለበት» ማሳሰባቸውንም የጥናቱ አስተባባሪ ዶክተር ጥላሁን ተፈራ አክለው ለዶቼ ቬለ በሰጡት ቃለ መጠይቅ አመልክተዋል። ጥናቱ ሁለት ዓመታትን የወሰደ ሲሆን ከትግራይ ክልል በቀር በሌሎቹ ክልሎች ላይ መደረጉ ተገልጿል።
3.6K viewsDW Amharic, 10:18
Open / Comment
2023-05-17 13:18:08
ሕገመንግሥትን የተመለከተ ጥናት ያካሄደው የኢትዮጵያ ፖሊሲ ተቋም በግኝቱ ኅብረተሰቡ አንድ ላይ ከመኖር የተለየ ሃሳብ እንደሌለው መረዳቱን አመለከተ። ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸው የጥናቱ አስተባባሪ ዶክተር ጥላሁን ተፈራ እንደተናገሩት፤ ትኩረት የተደረገባቸው የተመረጡት አንቀጾች አነጋጋሪዎች እና አነታራኪዎች ቢሆኑም በዚህ ጥናት የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የሚፈልጉት አብሮነትን መሆኑን ለመገንዘብ ተችሏል። የፌደራላዊት ሪፑብሊክ ኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን በተመለከተ ሦስት እሳቤዎች እንደሚታዩ ያመለከቱት ዶክተር ጥላሁን ፤ «አንዱ ይኽ ሕገ መንግሥት በምንም መልኩ መነካት የለበትም እንደውም ተጠናክሮ በደንብ ወደ መሬት መውረድ አለበት ሲል፤ ሌላኛው ጽንፍ ሕገ መንግሥቱ የተጻፈበትን ቀለም እንኳ ያህል ዋጋ የለውም ተቀዶ መጣል አለበት በሚል ያጣጥላል፤ ሦስተኛው ደግሞ ሕገ መንግሥቱ ጥሩ ነገሮች አሉት እነሱን ማስቀጠል፤ የሚሻሻሉ ካሉ ደግሞ እነሱን እያሻሻሉ መቀጠል እንጂ ከዜሮ መጀመር አስፈላጊ አይደለም» የሚል መሆኑን በመዘርዘር በዚህ መነሻነት ጥናቱ መካሄዱን ተናግረዋል። በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚታዩት ብሔር ተኮር ግጭቶች በዋነኛነት ሕገ መንግሥቱን ተጠያቂ የማድረግ አካሄድ ይታያል ያሉት የጥናቱ አስተባባሪ መንግሥትን እንደሚያማክር አንደ አንድ መንግሥታዊ ተቋም ልኂቃኑ እንደሚሉት ሕገ መንግሥቱ የችግሩ ሁሉ ምንጭ ነው ወይ የሚለውን ለመመልከት የኢትዮጵያ የፖሊሲ ተቋም ወደ ጥናቱ መግባቱንም አንስተዋል። ...
3.3K viewsDW Amharic, 10:18
Open / Comment
2023-05-16 20:54:02 https://p.dw.com/p/4RSUi?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
4.1K viewsDW Amharic, 17:54
Open / Comment
2023-05-16 20:17:07 Live stream finished (1 hour)
17:17
Open / Comment
2023-05-16 20:02:12 https://p.dw.com/p/4RSHX?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
4.1K viewsDW Amharic, 17:02
Open / Comment
2023-05-16 20:01:54 https://p.dw.com/p/4RRxs?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
3.5K viewsDW Amharic, 17:01
Open / Comment
2023-05-16 20:01:40 https://p.dw.com/p/4RS4r?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
3.2K viewsDW Amharic, 17:01
Open / Comment
2023-05-16 20:01:15 https://p.dw.com/p/4RRju?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
3.2K viewsDW Amharic, 17:01
Open / Comment