Get Mystery Box with random crypto!

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.34K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 591

2021-02-06 19:54:47 የአፍሪቃ ሕብረት መሪዎች ለሁለት ቀናት የሚዘልቅ ውይይታቸውን ዛሬ በኢንተርኔት ማካሄድ ጀምረዋል። መሪዎቹ አህጉሪቱን በሚመለከቱ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ጉዳዮች እና በወረርሽኙ ምክንያት ችላ የተባሉ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋናነት እንደሚወያዩ ተገልጿል። የዘንድሮው የመሪዎች ጉባኤ የተጀመረው ግብፅ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በሽታው በአፍሪቃ መገኘቱ ከተረጋገጠ ከአንድ ዓመት ገደማ በኋላ መሆኑ ነው። ወረርሽኙ በአህጉሪቱ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትል ይሆናል በሚል ተሰግቶ የነበረ ቢሆንም ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ጋር ሲነፃፀር በሽታውን ጥሩ በሚባል ደረጃ አፍሪቃ መቋቋሟ ተገልጿል። የአፍሪቃ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል (ሲዲሲ) እንደሚለው በዓለም ላይ በተህዋሲው ከተያዙት 3,5 በመቶ ያህሉ ብቻ ናቸው ከአፍሪቃ። በበሽታው ወይም በከሽታው ጋር በተያያዘ ሕይወታቸው ካለፉትም ቢሆን በአፍሪቃ የተመዘገበው አራት በመቶ ነው። እንዲያም ሆኖ በርካታ የአፍሪቃ ሃገራት የኮቪድ 19 ክትባት የሚያገኙበትን መንገድ በማመቻቸት ላይ ይገኛሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለም ላለፈው አንድ ዓመት የአፍሪቃ ሕብረት ሊቀመንበር ሆነው ያገለገሉት የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝደንት ስሪል ራማፎዛን በመተካት የዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቺሴ ኬዴ በይፋ ሥራቸውን ለመጀመር ተሰይመዋል። ራማፎዛም ዛሬ ከወንበራቸው በመነሳት ሥልጣኑንን አስረክበዋል።
« የሕብረታችንን ባንዲራ ለፕሬዚዳንት ቺሴ ኬዴ እያስረከብኩ ህብረታችንን ለመምራት ለሚወስዱት ኃላፊነት መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ።»
ከዚህም ሌላ የአፍሪቃ ሕብረት አባል ሃገራቱ በ34ተኛ ጉባኤያቸው የቀድሞው የቻድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሳ ፋኪ ማህማትን ዳግም የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር አድርገው መርጠዋል።
4.7K viewsDW Amharic, edited  16:54
Open / Comment