🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.90K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 586

2021-02-09 20:09:26 የፌደራል መንግስትና የተቃዋሚ ፖለቲከኞች በመቀሌ

የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት፣ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና የሐገር ሽማግሌዎች ሰሞኑን በተከታታይ የትግራይን ርዕሠ-ከተማ መቀሌን ጎብኝተዋል።
https://p.dw.com/p/3p7zs?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
3.7K viewsDW Amharic, 17:09
Open / Comment
2021-02-09 20:06:47 የአዉሮጳ ሕብረትና ትግራይ

የአዉሮጳ ሕብረት ባለስልጣናት ትግራይ ዉስጥ የተከሰተዉ ሰብአዊ ቀዉስና ባካባቢዉ ሊያስከትል የሚችለዉ ተፅዕኖ እንደሚያሳስባቸዉ አስታወቁ። የሕብረቱ የዉጪ ግንኙነት ኃላፊ፣የአስቸኳይ ርዳታ ኮሚሽነር እና የዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር በጋራ ባወጡት መግለጫ የርዳታ ድርጅቶች ወደ ትግራይ ክልል በሰፊዉ መግባት እንዲችሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ይፈቅድ ዘንድ ጠይቀዋል።
https://p.dw.com/p/3p82x?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
3.7K viewsDW Amharic, 17:06
Open / Comment
2021-02-09 20:03:57 የሀዋሳ ሀይቅን ለመታደግ የሚደረግ ዘመቻ

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በደለል ሙላት የተነሳ ህልውናው በአደጋ ላይ የሚገኘውን የሀዋሳ ሀይቅ ለመታደግ ያስችላል ያለውን የአካባቢ ጥበቃ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ።
https://p.dw.com/p/3p7qe?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
2.2K viewsDW Amharic, 17:03
Open / Comment
2021-02-09 20:01:22 የእነ አቶ ጃዋር ሞሐመድ የርሃብ አድማ

በማረሚያ ቤት በርሃብ አድማ ላይ የሚገኙት ፖሊቲከኞች እራሳቸውን እየሳቱ መሆኑን ቤተሰቦቻቸው እና ከጠበቆቻቸው አንዱ ለዶቼ ቨለ ተናገሩ::
https://p.dw.com/p/3p7qC?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
2.3K viewsDW Amharic, 17:01
Open / Comment
2021-02-09 18:57:33
ኢትዮጵያ እስከተያዘው የጎርጎርሳውያኑ 2021 መጨረሻ አንድ አምስተኛውን ህዝቧን የኮቪድ 19 ክትባት ለመከተብ ዝግጅት እያደረገች መሆኗን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንዳለው እስከ የፊታችን ሚያዝያ ወር የምትረከበውን 9 ሚሊዮን ጸረ ተህዋሲውን ክትባት ማዘዟን ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል። በዚህም እስከ የጎርጎርሳውያኑ የ2021 መጨረሻ ድረስ 20 በመቶ የሚሆነውን የሕብረተሰብ ክፍል ክትባቱን ተደራሽ ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን ሚኒስትሯ ለሮይተርስ የዜና ምንጭ ገልጸዋል። ሀገሪቱ «የጸረ ተህዋሲውን ክትባት በእርዳታ ማግኘት በሚያስችላት ሁኔታ ላይ ስትሰራ ነበር» ያሉት ሚንስትሯ ነገር ግን ክትባቱን ኮቫክስ በተባለው እና ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር በመሆን ደሃ ሀገራት ክትባቱን በፍትሃዊነት እንዲያገኙ በሚሰራ ጥምረት በኩል በኩል ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ነገር ግን በኮቫክስ በኩል ይቀርባል የተባለው ክትባት የትኛው እንደሆነ ዶ/ር ሊያ ያሉት ነገር የለም ። ኢትዮጵያ የጸረ ተህዋሲውን ክትባት በግዢ ለማቅረብ 328 ሚሊዮን ዶላር ወይም 13 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልጋት መንግስታዊው የዜና ምንጭ ኢዜአ ዘግቧል። በኢትዮጵያ 142,000 ሰዎች በኮሮና ሲያዙ 2100 የሚሆኑት ደግሞ ከኮሮና ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን አጥተዋል። የተቀረው ዓለም ክትባቱን በዘመቻ መስጠት በጀመረበት በዚህ ጊዜ አፍሪቃ 1,3 ቢሊዮን ለሚሆነው ህዝቧ ክትባቱን ለማድረስ ብርቱ ጥረት ይጠይቃታል ተብሏል። በአህጉሪቱ የተሻለ አቅም ያላቸው ብቻ ክትባቱን ማግኘት መጀመራቸውን ዘገባው አመልክቷል።
3.0K viewsDW Amharic, edited  15:57
Open / Comment
2021-02-09 17:11:18
የሱዳኑ ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሀምዶክ 7 የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን በአዲሱ ካቢኔያቸው ውስጥ ማካተታቸው ተነገረ።ጠቅላይ ሚንስትሩ ባለፈው እሁድ የቀድሞዎቹን የካቢኔ አባላት ሚንስትሮችን ከበተኑ በኋላ ተቃዋሚዎችን ያካተቱበትን አዲሶቹን ሚንስትሮች ይፋ አድርገዋል። የተቃዋሚዎችን በካቢኔ አባላት ውስጥ ያካተቱት አብደላ ሀምዶክ ባለፈው ጥቅምት ወር የተደረሰው የሰላም ስምምነት አንድ አካል እንደሆነም ተዘግቧል።አካታች ነው በተባለለት በአዲሱ የሀምዶክ መንግስት ውስጥ ሁለት ሚንስትሮች ከወታደራሩ ቡድን መውሰዳቸውም ነው የተገለጸው። ነጻነት ለለውጥ የተሰኘው ኃይል ስብስብ አባላት የሆኑ እና የኦማር አልበሽርን መንግስት ገዝግዘው በመጣል ውስጥ ትልቅ ሚና ነበራቸው የተባለላቸው ሰዎች የአዲሱን መንግስት አብዛኛውን የካቢኔ ሚንስትርነት ወንበር ይዘዋል።በሹመቱ ውስጥ ከተካተቱት የሱዳን የመጨረሻው በዴሞክራሲያዊ መንገድ ጠቅላይ ተመርጠው የነበሩት ጠቅላይ ሚንስትር ሳዲቅ አል መሃዲ ሴት ልጅ መርዬም ሳዲቅ አል መሃዲ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሆነው ተሾመዋል። የአብደላ ሀምዶክ አዲሱ መንግስት ሱዳን ወደ ዴሞክራሲያዊ መንገድ ለምታደርገው ጉዞ ሊያግዛት እንደሚችል ዘገባዎች ያመለክታሉ።
3.8K viewsDW Amharic, 14:11
Open / Comment
2021-02-09 17:05:59
በኢትዮጵያ ወደ ሰሜንና ሰሜን ምዕራብ አንዳንድ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የአየር በረራ ተጀመረ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፈጥሮ ሰሞኑን ተፈጥሮ ነበር ባለው አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ምክንያት ተቋርጦ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ አብዛኞቹ ከተሞች የአየር በረራ ማቋረጡን አስታውቆ ነበር ። ነገር ግን ዛሬ እንደተሰማው ከአዲስ አበባ ባህርዳር፣ ጎንደር እና ላሊበላ የአየር በረራ ትናንት መጀመሩን አየር መንገዱና ተሳፋሪዎች ገልፀዋል፡፡
አንድ የአየር መንገዱ ባልደረባ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት ከአርብ ከሰኣት ጀምሮ ከአዲስ አበባ ባህር ዳር፣ ጎንደርና ላሊበላ ይደረጉ የነበሩ በረራዎች ተቋርጠው ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ የአየር ሁኔታው የተሰተካከለ በመሆኑ እሁድ ወደ ላሊበላ በረራ መጀመሩን፣ ባህርዳርና ጎንደር ደግሞ ትናንት ሰኞ የበረራ አገልግሎት መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡
አንድ ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ለመምጣት ሲጠባበቁ የነበሩ የአየር መንገዱ ደንበኛ ትናንት በረራ መጀመሩ ከአየር መንገዱ ተነግሯቸው በነበረው የበረራ መስተጓጎል በተፈጠረ ወረፋ በረራቸው ተዛውሮ ዛሬ ባሕር ዳር መግባታቸውን ለዶይቼ ቬለ በስልክ ተናግረዋል፡፡
የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ እንዳረጋገጠውም ከትናንትና ጀምሮ በባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ አውሮፕላኖች እየተነሱ ሲያርፉ ነበር፡፡
ሆኖም ያለው የአየር ሁኔታ ሞቃታማነቱን እየጨመረ ስለሚሄድ በቅርቡ ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ለውጥ ሊኖር እንደሚችል በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ አጀንሲ የባህር ዳር ቅርንጫፍ የትንበያና ትንተና ቡድን አስተባባሪ አቶ ጥላሁን ውቤ የትንበያ ሪፖርቶችን ጠቅሰው ተናግረዋል፡፡
6.4K viewsDW Amharic, 14:05
Open / Comment
2021-02-09 17:05:01
የአውሮጳ ህብረት ኤርትራ ወታድሮቿን ከትግራይ ክልል እንድታስወጣ አሳሰበ:: ሕብረቱ ከዚሕ ቀደም ቀደም ዩናይትድስቴትስ የስጠችውን ተመሳሳይ ማሳሰቢያ በመደገፍ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ዉስጥ መግባትበአካቢዉ ግጭት እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል ሲል ወቅሷል::የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታት <<የኤርትራ ወታደሮችበትግራዩ ጦርነት አልተሳተፉም >> ሲሉ የቀረበባቸውን ክስ በየፊናቸው ሲያስተባብሉ ቆይተዋል:: አሁንም የኤርትራው የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል የአዉሮጳ ሕብረትን ማሳሰቢያ አጣጥለዋል::
የአውሮጳ ህብረት ባወጣው መግለጫ እንዳለው የኤርትራ ወታደሮች ጣልቃ ገብነትን በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት የሚሰጧቸው የማስተባበያ አስተያየቶች እርስበእርሳቸው የሚጣረሱ ናቸዉ ብሏል:: ህብረቱ አያይዞም በትግራይ ክልል እየታየ ያለው ሰብአዊ ቀውስ የተለየ ትኩረት ሊያገኝ ይገባል ብሏልም የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ እንዲቀርብ ሁኔታዎችን እንዲያመቻችእና ለሰላማዊ ሰዎች እና ለስደተኞች ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቋል:: የኖርዌያውያን ስደተኞች ጉዳይ ምክር ቤት እንዳለው <<በትግራይ ክልል ኤርትራዉያን ስደተኞች በሠፈሩበት መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ለስደተኞቹ አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ህንጻዎች እና ሌሎች ቁሳቁሶች ወድመዋል::>> በተያያዘ 20,000 ስደተኞችን እንደያዘ በተነገረለት ሽመልባ ለተሰኘ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ሰብአዊ ድጋፍ ማድረስ አልተቻለምብሏል:: የኢትዮጵያ መንግሥት በአካባቢው የህወሃት ታጣቂዎች የደፈጣ ውግያ በመጀመራቸው ለሁለቱየመጠለያ ጣቢያዎች አስፈላጊውን እርዳታ ለማድረስ መቸግሩን የሀገሪቱ የስደተኞች መርጃ ኤጄንሲአስታውቋል::
3.6K viewsDW Amharic, 14:05
Open / Comment
2021-02-08 20:24:38 https://p.dw.com/p/3p4kg?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
5.5K viewsDW Amharic, 17:24
Open / Comment
2021-02-08 20:05:14 https://p.dw.com/p/3p4cY?maca=amh-Facebook-dw
5.4K viewsDW Amharic, 17:05
Open / Comment