Get Mystery Box with random crypto!

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.70K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 588

2021-02-08 19:34:08
በጀርመን ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ግዛቶች የጣለው የበረዶ ግግር መደብኛ የመጏጏዣ እንቅስቃሴን አስተጏጉሏል:: በሳምንቱ የስራ መጀመርያ ቀን ዛሬ ሰኞ ከማለዳ ጀምሮ በጣለው የበረዶ ውሽንፍር በእብዛኞቹ አካባቢዎች የባቡር እና የየብስ መጏጏዣዎች ተስተጏጉለዋል::
ትናንት እሁድ በጀርመን ኖርዝ ራየን ቬስትፋልያ ግዛት ብቻ 720 የአየር ሁኔታ ስጋት የስልክ ጥሪ መቀበሉን የግዛቲቱ ፖሊስ አስታውቋል:: በእለቱ ከአየር ጠባይ ጋር በተገናኘ ከ507 በላይ አደጋዎች ተመዝግበዋል:: በዚህም 37 መጠነኛ ጉዳቶች መድረሳቸው ተገልጿል::
በአውሮዻ እየበረታ የሄደው የክረምቱ የአየር ሁኔታ ከጀርመን ውጭ በቤልጅየም ኔዘርላንድስ እና እንግሊዝ በተመሳሳይ የመጏጏዣ እንቅስቃሴ ማስተጏጎሉ ተነግሯል:: በቀጣዮቹ ቀናት የበረዶ ውሽንፍሩ ተጠናክሮ በአብዛኞቹ የሰሜን አውሮዻ ሀገራት ሊወርድ እንደሚችል የአየር ሁኔታ ትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ::
2.4K viewsDW Amharic, 16:34
Open / Comment
2021-02-08 18:24:44 https://www.facebook.com/dw.amharic/videos/1621340441396096
2.9K viewsDW Amharic, 15:24
Open / Comment
2021-02-08 17:06:11 የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ጥሶ የገባው የሱዳን ጦር የፈጠረው ችግር የበለጠ ከመወሳሰቡ በፊት መንግስት እልባት እንዲፈልግለት ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት የተባለ ማህበር ጠየቀ፡፡
ማህበሩ ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው <<የሱዳን ጦር የአገራችንን ድንበር ተሸግሮ ረጅም ኪሎሜትር ዘልቆ ገብቷል>> ብሏል፡፡ በመሆኑም ችግሮቹ ከመወሳሰባቸው በፊት መንግሰት እልባት መፈለግ አለበት ሲሉ የህብረቱ ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ መሳፍንት መንግስቱ ጠይቀዋል፡፡
ባለፈው ዓመት ከደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ታፍነው ተወሰዱ ተማሪዎችን ጉዳይ በተመለከተም መንግስት ይፋዊ መግለጫ እንዲሰጥ ኃላፊው ጠይቀዋል፡፡
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና ከወለጋ ዞኖች አካባቢ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ነበሩበት ከመመለሳቸው በፊት መንግስት አስተማማኝ ዋስትና እንዲሰጣቸውም ህብረት ጨምሮ አሳስቧል፡፡
3.7K viewsDW Amharic, 14:06
Open / Comment
2021-02-08 16:50:28
በቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ሰላምን ለማስፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ያግዛል የተባለለት እና ከወረዳ እስከ ክልል የሚገኙትን አመራሮች ያሳተፈ ጉባኤ በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ የቤኒንሻል ጉሙዝ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር ጉባኤው በመተከል ዞን የጸጥታ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የመተከል ዞን የጸጥታ ችግርን ለመቅረፍ ወደ ስራ የገባው የተቀናጀ ግብረ ሀይል ወደ ጫካ ሸሽተው የነበሩ 34ሺ የሚደርሱ የጉሙዝ ማህረሰብን ወደ ቀዬአቸው መመለስ መቻሉን ከዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በ151 ቀበሌዎችም የመንግስት መዋቅር በአዲስ መልክ መደራጀታቸውም ተገልጿል፡፡ በተደጋጋሚ የሚከሰተው የጸጥታ ችግርን በዘላቂነት በመፍታት የዜጎች ደህንነት ትኩረት እንዲሰጠው ማድረግ የጉባኤው ዓላማ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱል ቃድር ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ በዞኑ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር የአመራር ኃላፊነቱን በአግባቡ ባለመወጣቱ የተፈጠረ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በጉባኤው ላይ የማጥራት ስራም ይከናወናል ብለዋል፡፡
3.8K viewsDW Amharic, 13:50
Open / Comment
2021-02-08 16:03:50
You sent Today at 1:19 PM
በአማራ ክልል በወሊድ ወቅት የደም መፍሰስ ለእናቶች ሞት ምክንያት ሆኖ መቀጠሉ ተገልጧል:: ባለፉት 6 ወራት ከአንድ ሺህ 300 በላይ ህፃናት ከተወለዱ በኋላ ህይወታቸው እንዳለፈም ተመልክቷል:: አንዳንድ ባለሙያዎች የችግሮች ሁሉ መነሻ ለአዋላጅነት ሙያ የተሰጠው ትኩረትና ግንዛቤ አናሳ መሆንና በሙያው የመቆየት ፍላጎት አለመኖር እንዲሁም የግብዓት እጥረት ዋናዎቹ ምክንያቶች መሆናቸውን ይገልፃሉ፡፡
የኢትዮጵያ አዋላጅ ነርሶች ማህበር ሰሞኑን በባሕር ዳር ከተማ ባዘጋጀው ውይይት እንደተጠቀሰው የእናቶች እና የጨቅላ ህፃናት ሞት በተለያዩ ሁኔታዎች አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡
በእለቱ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት በአማራ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች ጤና አገልግሎት አስተባባሪ ሲሰተር አዲስዓለም ጫኔ እንዳሉት አሁንም በተለያዩ ምክንያቶች ከሚሞቱ እናቶች ውስጥ 43 ከመቶ የሚሆኑት ህይወታቸው የሚያልፈው በወሊድ ወቅት በሚፈጠር ደም መፍሰስ ነው፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት 74 ከመቶ የሚሆኑት ህፃናት ሆስፒታል ውስጥ የተወለዱ ቢሆንም ከሚሞቱት መካከል በርካቶቹ ደግሞ እዛው ሆስፒታል ውስጥ እንደሚሞቱ በቀረበው ፅሁፍ ቀርቧል፡፡ ይህ እንዴት ሊሆን እንደቻለ ሲሰተር አዲስዓከለምን በሰጡት ምላሽ የሆስፒታሎቹ የመሰረተ ልማት እጥረትና ሆስፒታሎች በርካታ ተገልጋዮችን ስለሚያስተናግዱ ከሚፈጠር ጫና ነው ብለዋል፡፡
በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶች ቁጥር አሁንም ወደ ተፈለገው ደረጃ እንዳልደረሰ ያመለከቱት ባለሙያዋ፣ 48 ከመቶዎቹ አሁንም ወደ ጤና ተቋማት አይመጡም፡፡
ችግሮቹ በርካታ መሆናቸውን የሚናገሩት ባለሙያዎቹ የግብዓት እጥረት ዋነኛው ነው፡፡
የክፍያና የትምህርት እድሎች አለመኖርና ለአዋላጅ ነርስነት የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን ሌላው ችግር መሆኑን የሚናገሩት ባለሙያዎቹ ብዙዎቹ
4.1K viewsDW Amharic, 13:03
Open / Comment
2021-02-07 20:22:14 ሞቃዲሾ-ቦምብ ፈንድቶ 12 የስለላ ሠራተኞች ተገደሉ

ሶማሊያ ዉስጥ ዱሳማሬብ በተባለችዉ ከተማ አጠገብ መንገድ ዳር የተቀበረ ፈንጂ 12 የመረጃ ወይም የስለላ ሠራተኞችን ገደለ። ዱሳማሬብ የሶማሊያ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞች ነገ ሊደረግ ታቅዶ ስለነበረዉ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ለመነጋገር ተሰብስበዉባት የነበረች ከተማ ናት። ፖሊስ እንዳስታወቀዉ በአደጋዉ ከተገደሉት የስለላ ሠራተኞች መሐል አንዱ በከተማይቱ የሶማሊያ ብሔራዊ የመረጃና የፀጥታ መስሪያ ቤት ኃላፊ ነበሩ።ቦምቡን ያጠመደዉ የሶማሊያዉ አክራሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ መሆኑን ቡድኑ አምኗል። ታዛቢዎች እንደሚሉት የሶማሊያ ፖለቲከኞች የገጠሙትን ዉዝግብ አሸባብ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ይመለከተዋል።
6.1K viewsDW Amharic, 17:22
Open / Comment
2021-02-07 20:21:58 https://p.dw.com/p/3p1S0?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
6.0K viewsDW Amharic, 17:21
Open / Comment
2021-02-07 20:21:36 ሎክናዉ-ሕንድ-የበረዶ ክምር ተንዶ ብዙ አካባቢ አጥለቀለቀ

ሰሜናዊ ሕንድ በሚገኙ ተራራዎች ላይ የተከመረ በረዶ ተንዶ ሁለት የኤልክትሪክ ማመንጫ ግድቦችንና በርካታ መኖሪያ ቤቶችን ጠራርጎ ወሰደ። ዛሬ ሲነጋጋ የተናደዉ በረዶ ዝቅተኛ ቦታዎች የሚገኙ በርካታ አካባቢዎችን በጎርፋና ጭቃ አጥለቅልቋቸዋል። አደጋዉ የደረሰባት የኡታራካሐድ ግዛት አገረ-ገዢ ትሪቬንድራ ሲንጌሕ ራዋት እንዳሉት ጎርፉ ሰባት ሰዎች መግደሉ ተረጋግጧል። ሌሎች 125 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም።
2.5K viewsDW Amharic, 17:21
Open / Comment
2021-02-07 20:21:13 https://p.dw.com/p/3p1ct?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
2.5K viewsDW Amharic, 17:21
Open / Comment
2021-02-07 20:20:52 https://p.dw.com/p/3p1Sp?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwamharicbot
2.3K viewsDW Amharic, 17:20
Open / Comment