🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.70K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 13

2023-05-03 20:12:47 https://p.dw.com/p/4QrGW?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
3.0K viewsDW Amharic, 17:12
Open / Comment
2023-05-03 20:11:05 https://p.dw.com/p/4QqJb?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
3.0K viewsDW Amharic, 17:11
Open / Comment
2023-05-03 20:10:29 https://p.dw.com/p/4QrHY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
3.0K viewsDW Amharic, 17:10
Open / Comment
2023-05-03 20:00:11 Live stream finished (1 hour)
17:00
Open / Comment
2023-05-03 18:19:39
በትግራይ ክልል የሰብአዊ አቅርቦት ካቆመ ከ20 ቀናት በላይ ተቆጠረ

የዓለም ምግብ ድርጅት ለትግራይ ክልል የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ካቆመ ከ20 ቀናት በላይ ማለፉን የክልሉ አስተዳደር ዐስታወቀ ። የክልሉ የአደጋ መከላከል ኮሚሽን፦ ለትግራይ ክልል ይላክ የነበረው ሰብአዊ ርዳታ መቋረጡን «አስደንጋጭ» ብሎታል ። ከ6 ሚልዮን በላይ የሚገመት በትግራይ ክልል ያለ ርዳታ ፈላጊ ሕይወትንም አደጋ ላይ የሚጥል ሲል ገልጿታል ።

ትናንት ከዓለም የምግብ ድርጅት በኩል የተሰማው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ተቋሙ ለትግራይ ክልል የሚሰጠውን የምግብ ርዳታ ያቋረጠው ለችግረኞች መከፋፈል ይገባው የነበረ እህል በተደጋጋሚ በመዘረፉ እና በመሸጡ ነው ። በዚህ ጉዳይ ዙርያ ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት በትግራይ ክልል አደጋ መከላከል ኮሚሽን የአስቸኳይ ምላሽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብረእግዚአብሔር አረጋዊ፦ የዓለም የምግብ ድርጅትን ጨምሮ ሌሎች ተቋማት የሚያቀርቡትን የምግብ ድጋፍ ካቋረጡ 20 ቀናት እንዳለፈ ጠቁመዋል ። በትግራይ ክልል የርዳታ እህል በተደጋጋሚ ስለመዘረፉም ተናግረዋል ። ክልሉ በተለያዩ ኃይሎች እየተዳደረ መሆኑን በመግለጽም ለዝርፊያው የውጭ ኃይሎች እጅ አለበት ብለዋል።

በመቐለ ከተማ ገበያዎች በትግራይ ክልል የማይከፋፈል የዓለም ምግብ ድርጅት አርማ ያላቸው የምግብ አይነቶች ጭምር ሲሸጡ እንደሚስተዋል ግን ጠቁመዋል ...

ዘገባ፦ሚሊዮን ኃይለሥላሴ ከመቐለ፤ ዶይቸ ቬለ (DW) https://www.facebook.com/dw.amharic/posts/pfbid0uhwFKg7M3pacxiFeSLTQwHytUxkbmbQGyWKz6GK5ok95VzT67PBEzdyddZhGvVZbl
3.8K viewsDW Amharic, 15:19
Open / Comment
2023-05-03 17:40:07
በዓለም ዙሪያ ከሩብ ቢሊዮን በላይ ሰዎች በ2022 ተርበዋል

የተባበሩት መንግሥታት የዓለም መርኃ ግብር ዛሬ ይፋ ባደረገው «የ2023 የዓለም የምግብ ቀውስ ሠነድ» መሰረት ከስድስት ወራት በፊት በተደረገ ጥናት በዓለም ዙሪያ 258 ሚሊዮን ሰዎች ተርበዋል ። የዓለም አቀፍ ድርጅትቱ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬሽ፦ «ከሩብ ቢሊዮን በላይ ሰዎች ለብርቱ ረሐብ ተጋልጠዋል፤ እንደውም ከፊሉ ወደ ጠኔ አፋፍ ተጠግተዋል» ሲሉ ተናገግረዋል ። እንደ ድርጅቱ መግለጫ ከሆነ፦ በዓለም ዙሪያ በ58 ሃገራት የሚገኝ ከሩብ ቢሊዮን በላይ ሕዝብ በጎርጎሪዮሱ አቆጣጠር 2022 ለአጣዳፊ የምግብ ዋስትና እጦት ተጋልጦ ቆይቷል ።

ከተጠቀሰው አሐዝ ከዐርባ በመቶ በላይ ብርቱ የምግብ ችግር ያጋጠመባቸው ተብለው ከተጠቀሱ አምስት ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ ትገኝበታለች ። የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፤ አፍጋኒስታን፤ ናይጄሪያ እና የመንም በየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሠነድ ከተጠቀሱት ሃገራት ይገኙበታል ።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና በአውሮጳ ኅብረት የተቋቋመው የሰብዓዊ ድርጅቶች ኅብረት የዓለም የምግብ ቀውሶች ዘገባ እንዳመለከተው በጎርጎሪዮሱ አቆጣጠር 2022 በሶማሊያ፣ በአፍጋኒስታን፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ሄይቲ፣ ናይጀሪያ ፣ደቡብ ሱዳንና የመን ደግሞ ሰዎች ለሞትና ለጠና ረሃብ ተዳርገዋል ። በጎርጎሪዮሱ አቆጣጠር 2022 ከኢትዮጵያ እና ከዚምባብዌ ግን ሙሉ መረጃ አለመገኘቱንም ሠነዱ ይጠቅሳል ።

የምስል መረጃ፦ የ2023 የዓለም የምግብ ቀውስ ሠነድ
3.8K viewsDW Amharic, 14:40
Open / Comment
2023-05-03 16:33:56
ኦሮሚያ ክልል በደቦ ፍርድ ኢሰብአዊ ድርጊት ፈጸሙ የተባሉ ተያዙ

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ ሃርወዩ በምትባል ቀበሌ ሁለት ወጣቶች ላይ ኢሰብአዊ ርምጃ የወሰዱ የተባሉ ባለስልጣናት መታሰራቸው ተገለጸ ። በአከባቢው ሰሞኑን ሁለት ወጣቶች እጅ እግራቸውን የፊጢኝ ወደኋላ ታስረው ሲደበደቡና ሲሰቃዩ የሚያሳይ ምስል በማኅበራዊ መገናኛ ተለቅቆ መነጋገሪያ ሆኗል ። ጃሮ ዳሌ እና ጋርቦሌ ዋቆ በተባሉ ሁለት ወጣቶች ላይ የተፈፀመው የደቦ ፍርድ በሚል በሰብአዊ መብት ጥሰት ተተችቷል ።

የያቤሎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጎቡ ጫና በተለይም ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት፤ በዚህ ሰብአዊ መብትን በጣሰው ድርጊት የተሳተፉት ከቀበሌ አስተዳዳሪ እስከ የአከባቢውን ሰላም እንዲያስጠብቁ የታጠቁ ሚሊሻዎች ያሉት ናቸው ብለዋል ።
በመሆኑም ወጣቶቹን ይዘው ያለ ፍርድ አስረው በማሰቃየት ድርጊት የተጠረጠሩ እስከ ዛሬ የቀበሌ አስተዳዳሪ እና ታጣቂ ሚሊሻዎችን ጨምሮ ዐሥር ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ለፍረድ እየቀረቡ ነው ሲሉ ገልፀዋል ።

አንደ ኃላፊው ገለጻ ለችግሩ መነሻ የሆነው በቀበሌው 6 ኩንታል የርዳታ እህል ጠፍቶ በገበያ መሸጡና በዚህም ስርቆት ሁለቱ ወጣቶች መጠርጠራቸው ነው ። ሁለቱ ለድብደባ እና ስቃዩ የተዳረጉት ወጣቶች አንዱ የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ እረኛ ነው ተብሏል ።

የወረዳው አስተዳዳሪ ድብደባው የተፈፀመባቸው ሁለቱ ወጣቶች አሁን በደህና ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙና እነሱን የሚያስከስስ መረጃ አለመኖሩንም አንስተዋል ።
ስለጉዳዩ የተጠየቀው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ መረጃ እያሰባሰብኩ ነው ብሏል፡፡

ዘገባ፦ሥዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ፤ ዶይቸ ቬለ (DW)
4.1K viewsDW Amharic, 13:33
Open / Comment
2023-05-03 14:46:15
በታንዛኒያው ድርድር ስምምነት ላይ አለመደረሱ ተገለጠ
የኢትዮጵያ መንግሥትና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (OLA) ብሎ በሚጠራው መንግሥት «ሸኔ» በሚለው ታጣቂ ቡድን መካከል ታንዛኒያ ውስጥ ሲካሄድ የነበረው ድርድር «የመጀመሪያ ምእራፍ» ያለስምምነት መጠናቀቁ ተገለጸ ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ በይፋዊ የማኅበራዊ መገናኛ አውታሩ ላይ ባወጣው ቁጥብ መግለጫ «ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ቢሆንም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው ምእራፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ አልተቻለም» ብሏል ። አወንታዊ የተባሉትም ሆነ ስምምነት ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች የትኞቹ እንደሆኑ ግን በግልጽ አልተቀመጠም ።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት «የሰላም» ያለው ውይይት ታንዛኒያ ውስጥ መከናወኑን ከመግለጽ ባሻገር ግን ውይይቱ በማን እና በማን መካከል እንዲሁም በየትኞቹ ጉዳዮች መኪያሄዱን አልጠቀሰም ። ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፦ (OLF-OLA press Release በሚል) ከሳምንት በፊት ባወጣው መግለጫ የድርጅቱ መጠሪያ «የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት» እንደሆነ እና ከዚህ ሌላ ማንኛውንም ስያሜ እንደማይቀበል በመግለጫው አስታውቆ ነበር ። በዛሬው መግለጫው መንግስት አንዳችም ስያሜ አልጠተቀመም ።
ይህ ጽሑፍ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በታጣቂ ቡድኑ በኩል ስለድርድሩ በይፋ የወጣ መረጃ የለም ። ለቡድኑ ቅርበት ያላቸው የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ግን ቁልፍ በሆኑ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ መስማማት አለመቻላቸውን ዘግበዋል ።
https://www.facebook.com/dw.amharic/posts/pfbid0245pnragAzXExxbYfcPZwDz7fteKzF8QKJYxdDxdP1Mnpe5AS9LHJtQeQHRrSMtfl
4.3K viewsDW Amharic, 11:46
Open / Comment
2023-05-03 13:54:05 https://p.dw.com/p/4QpwY?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
4.0K viewsDW Amharic, 10:54
Open / Comment
2023-05-03 13:34:59
ታጣቂዎች ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትጥቅ አስረከቡ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በመተከል ዞን ውስጥ በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች ውስጥ 72 የሚደርሱት የታጠቁ እና ሌሎች ድጋፍ ሲያደርጉላቸው የነበሩ 18 በድምሩ 90 የታጣቂ ቡድኑ አባላት በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ በሚል ትጥቃቸውን ለመንግስት ማስረከባቸውን ዐስታወቀ ። ታጣቂዎቹ በዞኑ ጉባ እና ዳንጉር ወረዳዎች ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሲሆን፤ የሰላም ጥሪ ተቀብለው ተመለሱ የተባለው ትናንት ማምሻውን እንደሆነም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀሩን ኡመር ለዶይቸ ቬለ (DW) ተናግረዋል ። በጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሥር የሚንቀሳቀሱ ናቸው ተብሏል ።

የመተከል ዞን ለረጅም ጊዜ በጊዜያዊ አስተዳደር ወይንም ኮማንድ ፖስት ሲተዳደር የቆየ ሲሆን፤ በታጣቂዎች እንቅስቃሴ እና የተለያዩ ጥቃቶች ምክንያት በዞኑ ብቻ ከ2 መቶ 60 ሺ በላይ ዜጎች ተፈናቅለው ቆይተዋል ። በዞኑ በእጀባ ይሰጥ የነበረው የመጓጓዣ አገልግሎት በአሁኑ ወቅት መንገዶች ሙሉ በሙሉ ተከፍተው አገልግሎቱ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መመለሱንም ኮሚሽነሩ አስረድተዋል ።

የጉሙዝ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉዴታ ከክልሉ መንግስት ጋር ስምምነት ከተደረገ ጥቅምት 9 ቀን፣ 2015 ዓ.ም ወዲህ በድርጅቱ ስም ታጥቀው ይንቀሳቀሱ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችት ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ኅብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ተናግረዋል ። የሰላም ጥሪውን የማይቀበሉ ታጣቂዎች ድርጅቱን እንደማይወክሉ እና ኃላፊነትም እንደማይስዱ ተናግረዋል ።

ዘገባ፦ ነጋሣ ደሳለኝ ከአሶሳ፤ ዶይቸ ቬለ (DW)
https://www.facebook.com/dw.amharic/posts/pfbid033uKsmRw2yCN9ABQqwEkoPyTD2Y19LyjBazRwareKymXUzEjkBo6LqWTV2Du6nkzql
4.1K viewsDW Amharic, edited  10:34
Open / Comment